YouVersion Logo
Search Icon

የዘላለም ሕይወትSample

የዘላለም ሕይወት

DAY 1 OF 9

እውነተኛ ሕይወት የሚገኘው ከኢየሱስ ነው።

ጌታ ኢየሱስ ስለአገልግሎቱ ሲናገር ዓላማው ለሰዎች የዘላለም ሕይወት መስጠት እንደሆነ ተናግሯል። "በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስከ መስጠት ድረስ ዓለምን እንዲሁ ወድዷልና" (ዮሐንስ 3:16)።

ጌታ ኢየሱስ ሊሰጠን የሚፈልገው ሕይወት ዘላለማዊ ነው። አንዳንድ ሰዎች እንደሚገምቱት ክርስትና የአምልኮ ሥርዓቶችና ሕጎችን የመፈጸም ግዴታና፣ ደስታ የሌለበት አሰልቺ ሕይወት አይደለም። ጌታ ኢየሱስ በአምላክ ፊት ለእኛና ላመኑት ሁሉ ሙሉ ደስታ ያለበት የዘላለም ሕይወት አቅርቦልናል። ''የሕይወትን መንገድ ታሳየኛለህ፤ በአንተ ዘንድ የደስታ ሙላት፣ በቀኝህም የዘላለም ፍስሐ አለ'' (መዝሙር 16:11)።

የራሱን ሕይወት በመስጠት ጌታ ኢየሱስ ይህን ዘላለማዊና የተባረከ ሕይወት ሰጥቶናል። በዮሐንስ 10፡15 ላይ እንደተጻፈው፣ ''ይህም አብ እኔን እንደሚያውቀኝ እኔም አብን እንደማውቀው ነው። ሕይወቴንም ስለ በጎቼ አሳልፌ እሰጣለሁ።'' ይህም የመጨረሻው የፍቅር ተግባር ነው። የእግዚአብሔር ልጅ ሰው ለመሆን እና ነፍሱን ለኃጢአተኞች አሳልፎ ለመስጠት የተዘጋጀ ነበር። ይህንንም ያደረገው በራሱ ፈቃደኝነት ነው (ዮሐንስ 10፡ ይመልከቱ)። ኢየሱስ ሞትን በሞቱ በማሸነፍ በእርሱ ለሚያምኑ ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖራቸው አድርጓል።

ጌታ ኢየሱስ የሚሰጠውን ይህን ሕይወት ይፈልጋሉ?

About this Plan

የዘላለም ሕይወት

ጌታ ኢየሱስ ስለ አገልግሎቱ ሲናገር ዓላማው ለሰዎች የዘላለም ሕይወት መስጠት እንደሆነ ተናግሯል። “በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ” (ዮሐ. 3፡16)። ይህ የዘላለም ሕይወት ምንድን ነው? መጽሐፍ ቅዱስ ስለዚህ የዘላለም ሕይወት ምን እንደሚል እንመልከት።

More