የዘላለም ሕይወትSample

እውነተኛ ሕይወት የሚገኘው ከኢየሱስ ነው።
ጌታ ኢየሱስ ስለአገልግሎቱ ሲናገር ዓላማው ለሰዎች የዘላለም ሕይወት መስጠት እንደሆነ ተናግሯል። "በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስከ መስጠት ድረስ ዓለምን እንዲሁ ወድዷልና" (ዮሐንስ 3:16)።
ጌታ ኢየሱስ ሊሰጠን የሚፈልገው ሕይወት ዘላለማዊ ነው። አንዳንድ ሰዎች እንደሚገምቱት ክርስትና የአምልኮ ሥርዓቶችና ሕጎችን የመፈጸም ግዴታና፣ ደስታ የሌለበት አሰልቺ ሕይወት አይደለም። ጌታ ኢየሱስ በአምላክ ፊት ለእኛና ላመኑት ሁሉ ሙሉ ደስታ ያለበት የዘላለም ሕይወት አቅርቦልናል። ''የሕይወትን መንገድ ታሳየኛለህ፤ በአንተ ዘንድ የደስታ ሙላት፣ በቀኝህም የዘላለም ፍስሐ አለ'' (መዝሙር 16:11)።
የራሱን ሕይወት በመስጠት ጌታ ኢየሱስ ይህን ዘላለማዊና የተባረከ ሕይወት ሰጥቶናል። በዮሐንስ 10፡15 ላይ እንደተጻፈው፣ ''ይህም አብ እኔን እንደሚያውቀኝ እኔም አብን እንደማውቀው ነው። ሕይወቴንም ስለ በጎቼ አሳልፌ እሰጣለሁ።'' ይህም የመጨረሻው የፍቅር ተግባር ነው። የእግዚአብሔር ልጅ ሰው ለመሆን እና ነፍሱን ለኃጢአተኞች አሳልፎ ለመስጠት የተዘጋጀ ነበር። ይህንንም ያደረገው በራሱ ፈቃደኝነት ነው (ዮሐንስ 10፡ ይመልከቱ)። ኢየሱስ ሞትን በሞቱ በማሸነፍ በእርሱ ለሚያምኑ ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖራቸው አድርጓል።
ጌታ ኢየሱስ የሚሰጠውን ይህን ሕይወት ይፈልጋሉ?
Scripture
About this Plan

ጌታ ኢየሱስ ስለ አገልግሎቱ ሲናገር ዓላማው ለሰዎች የዘላለም ሕይወት መስጠት እንደሆነ ተናግሯል። “በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ” (ዮሐ. 3፡16)። ይህ የዘላለም ሕይወት ምንድን ነው? መጽሐፍ ቅዱስ ስለዚህ የዘላለም ሕይወት ምን እንደሚል እንመልከት።
More
Related Plans

Whiskers & Prayers: Devotionals for Cat Lovers

Note to Self: Helpful Reminders for Healthier Relationships

Wellness Wahala: Faith, Fire, and Favor on Diplomatic Duty

Start Strong: 7 Prayers for Bold New Beginnings

Heart of Worship

LIVE BOLDLY: Embracing the Abundant Life You Were Born for - Embracing the Abundant Life You Were Born For

The Unworthy Parent: God’s Grace in Your Gaps

HEAL BOLDLY: Healing Is Holy Work - a 5-Day Devotional Journey for Women Ready to Heal, Grow, and Rise

Consciousness of God's Presence
