የዘላለም ሕይወትSample

በአዲሱ ምድር ላይ ሀጢያት የለም።
የዘላለም ሕይወት ዋናው ነገር ከእግዚአብሔር ሃሳብ ጋር ተስማምቶ መኖር ሲሆን፣ ከእግዚአብሔር ጋር በማመፅ ለሚኖሩ ሰዎች አይደለም። የኃጢአት ይቅርታ እና ጌትነቱን ያልተቀበሉ፤ በኃጢአተኛ አኗኗራቸው የጸኑ ሰዎች የዘላለም ሞት ይጠብቃቸዋል። ይህ በዚህ ምድር ላይ የምርጫቸው ውጤት ሲሆን፤ ማንም ሰው አሁን ከእግዚአብሔር ጋር መኖር የማይፈልግ፣ ለዘላለም ከእርሱ ጋር ሊኖር አይችልም።
የዘላለም ሕይወት ፍጹም የሆነ ሕይወትን ለኖሩ ሰዎች ብቻ አይደለም። ያ ቢሆን ኖሮ አንድም ሰው ብቁ አይሆንም ነበር። ሁላችንም እግዚአብሔርን በድለናል፣ ኃጢአተኛ ሆነን ተወልደናል። ዳዊት በመዝሙሩ “እነሆ በዓመፅ ተወልጃለሁ እናቴም በኃጢአት ወለደችኝ” (መዝሙር 51፡5)።
ዋናው ነገር ኃጢአታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ደም ታጥቦ መወገዱ ነው ( ራዕይ 7፡14)። ከኃጢዓታችን ንስሐ ከገባን እና ጌታ ኢየሱስን እንደ ጌታችን እና አዳኛችን ከተቀበልን እግዚአብሔር ኃጢአታችንን ይቅር ይላል። እርሱ "ተመልሰህ ትራራልናለህ፤ ኀጢአታችንን በእግርህ ትረግጣለህ፤ በደላችንንም ሁሉ ወደ ጥልቁ ባሕር ትጥላለህ"( ሚክያስ 7፡19)።
ከፈተናና ከኃጢአት ጋር ለሚታገሉ አማኞች ሁሉ ይህ ትልቅ ተስፋ ነው! በአዲሱ ምድር ላይ ኃጢአት ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ድል ይደረጋል።
ከኃጢአት ነጻ ለመሆን ትፈልጋለህ?
Scripture
About this Plan

ጌታ ኢየሱስ ስለ አገልግሎቱ ሲናገር ዓላማው ለሰዎች የዘላለም ሕይወት መስጠት እንደሆነ ተናግሯል። “በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ” (ዮሐ. 3፡16)። ይህ የዘላለም ሕይወት ምንድን ነው? መጽሐፍ ቅዱስ ስለዚህ የዘላለም ሕይወት ምን እንደሚል እንመልከት።
More
Related Plans

40 Rockets Tips - Workplace Evangelism (31-37)

Built for Impact

Sowing God's Word

A Mother's Heart

Multivitamins - Fuel Your Faith in 5-Minutes (Pt. 3)

Peter, James, and John – 3-Day Devotional

Live the Word: 3 Days With Scripture

Connecting With the Heart of Your Child

Moses: A Journey of Faith and Freedom
