የዘላለም ሕይወትSample

ሰውነታችንም ይታደሳል።
ትላንት የሥጋ ሞት የዘላለምን ሕይወትን እንደማያቋርጥ አይተናል። ይህ ማለት ሰውነታችን አስፈላጊ አይደለም ወይም ከእግዚአብሔር የወደፊት ፈቃዱ ጋር ምንም ግንኙነት የለውም ማለት አይደለም።
ጌታ ኢየሱስ የሰው ልጆችን ለመፍረድና አዲስ ምድርን ለመፍጠር ሲመለስ የእኛም አካል ይነሣል። ከትንሣኤ በኋላ የክርስቶስን ክቡር ሥጋ ለመምሰል ይለወጣል፤ የማይሞት እና የማይበሰብስ ሆኖ ይነሳል።
ሐዋርያው ጳውሎስ ይህንን ከዘር ከመዝራት ጋር አመሳስሎታል። ሟች አካላችን በድካምና በውርደት የተዘራ ነው፤ ሁላችንም በቀብር ሥነ ሥርዓት ላይ እንደምናውቀው፣ የሞተና የሚበሰብስ አካል ክብር ባይኖረውም፤ ሰውነታችን በክብር ይነሳና ከመንፈሳችን ጋር እንደገና በአምላካችን አዲሱ ምድር ላይ ለዘላለም ይኖራል።
ይህን ዘላለማዊነት ከአመላካችን ከእግዚአብሔር ጋር የምንሆነው በመንፈሳዊነት ብቻ ሳይሆን፤ በተለወጠ አካል እና በንጹህ መንፈስ በመሆናችን ነው። እግዚአብሔር አምላክ ለሰውነታችን ዋጋ በመስጠቱ እንዲታደስ እንጂ እንዲጠፋ አይፈልግም።
እርሶስ ለሰውነትዎ ዋጋ ይሰጣሉ?
About this Plan

ጌታ ኢየሱስ ስለ አገልግሎቱ ሲናገር ዓላማው ለሰዎች የዘላለም ሕይወት መስጠት እንደሆነ ተናግሯል። “በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ” (ዮሐ. 3፡16)። ይህ የዘላለም ሕይወት ምንድን ነው? መጽሐፍ ቅዱስ ስለዚህ የዘላለም ሕይወት ምን እንደሚል እንመልከት።
More
Related Plans

Returning Home: A Journey of Grace Through the Parable of the Prodigal Son

Unapologetically Sold Out: 7 Days of Prayers for Millennials to Live Whole-Heartedly Committed to Jesus Christ

Homesick for Heaven

Greatest Journey!

Stormproof

Let Us Pray

Faith in Hard Times

Breath & Blueprint: Your Creative Awakening

God in 60 Seconds - Basic Bible Bites
