የዘላለም ሕይወትSample

በአዲሱ ምድር ላይ ሞት እና ስቃይ የለም።
እግዚአብሔር አምላክ ለአዳም እና ሔዋን አስቀድሞ እንዳስጠነቀቃቸው፤ በእርሱ ላይ ባመፁ ጊዜ ኃጢአታቸው ሥቃይና ሞትን አስከትሏል። ‘’የኀጢአት ደመወዝ ሞት ነውና" ( ሮሜ 6:23)።
ከዚያን ጊዜ ጀምሮ መከራ እና ስቃይ የሰው የሕይወት ክፍል ሆኗል። አንዳንዶቹ ስቃዮች በሰዎች የሚከሰቱ፣ ሌሎች ዓይነት መከራዎች ደግሞ በዚህ ዓለም ውድቀት ወይም በራሳችን የተሳሳተ የሕይወት ምርጫ የመጡ ናቸው። በዚህም ምክንያት ከጽጌረዳ አበባ እሾህ በላይ ሕይወት በመከራ የተሞላ ሆነ። ሙሴ እንኳን አማረረ፡- "የዕድሜያችን ዘመን ሰባ ዓመት፣ ቢበዛም ሰማንያ ነው፤ ከዚያ በላይ ከሆነም ድካምና መከራ ብቻ ነው" (መዝሙረ ዳዊት 90:10)።
ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ የኃጢአትን ዋጋ ለሰው ዘር ሁሉ ሲከፍል፤ የኃጢአት ውጤት የሆነውን ሞትን አሸንፏል። በኢሳይያስ 25፡8 ላይ ጌታ ''ሞትን ለዘላለም እንደሚውጥ'' እና ''ከፊት ሁሉ እንባን እንደሚያብስ'' የተስፋው ቃል ተፈጸመ። እነዚህ የኃጢአትና የውድቀት ውጤቶች የሆኑት፤ 'ኀዘን፣ ለቅሶ እና ሥቃይ' በዘላለም ክብሩ ውስጥ አይኖሩም።
ከአምላካችን ከእግዚአብሔር እና ካመኑት ወገኖቻችን ጋር በገነት ያለመከራ ለዘላለም መኖር እጅግ የሚያስደስት ህይውት ነው።
Scripture
About this Plan

ጌታ ኢየሱስ ስለ አገልግሎቱ ሲናገር ዓላማው ለሰዎች የዘላለም ሕይወት መስጠት እንደሆነ ተናግሯል። “በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ” (ዮሐ. 3፡16)። ይህ የዘላለም ሕይወት ምንድን ነው? መጽሐፍ ቅዱስ ስለዚህ የዘላለም ሕይወት ምን እንደሚል እንመልከት።
More
Related Plans

Whiskers & Prayers: Devotionals for Cat Lovers

Note to Self: Helpful Reminders for Healthier Relationships

Wellness Wahala: Faith, Fire, and Favor on Diplomatic Duty

Start Strong: 7 Prayers for Bold New Beginnings

Heart of Worship

LIVE BOLDLY: Embracing the Abundant Life You Were Born for - Embracing the Abundant Life You Were Born For

The Unworthy Parent: God’s Grace in Your Gaps

HEAL BOLDLY: Healing Is Holy Work - a 5-Day Devotional Journey for Women Ready to Heal, Grow, and Rise

Consciousness of God's Presence
