መዝሙር 148
148
መዝሙር 148
1ሃሌ ሉያ።#148፥1 አንዳንዶች ከ14 ጭምር እግዚአብሔር ይመስገን ይላሉ።
እግዚአብሔርን ከሰማያት አመስግኑት፤
በላይ በአርያም አመስግኑት።
2መላእክቱ ሁሉ አመስግኑት፤
ሰራዊቱ ሁሉ አመስግኑት፤
3ፀሓይና ጨረቃ አመስግኑት፤
የምታበሩ ከዋክብት ሁሉ አመስግኑት።
4ሰማየ ሰማያት አመስግኑት፤
ከሰማያትም በላይ ያላችሁ ውሆች አወድሱት።
5እርሱ ስላዘዘ ተፈጥረዋልና፣
የእግዚአብሔርን ስም ያመስግኑት።
6ከዘላለም እስከ ዘላለም አጸናቸው፤
የማይሻርም ሕግ ደነገገላቸው።
7የባሕር ውስጥ ግዙፍ ፍጥረትና ጥልቅ ውሆች ሁሉ፣
እግዚአብሔርን ከምድር አመስግኑት።
8እሳትና በረዶ፣ ዐመዳይና ጭጋግ፣
ትእዛዙንም የሚፈጽም ዐውሎ ነፋስ፣
9ተራሮችና ኰረብቶች ሁሉ፣
የፍሬ ዛፎችና ዝግቦች ሁሉ፣
10የዱር አራዊትና የቤት እንስሳት ሁሉ፣
በምድር የሚሳቡ ፍጥረታትና የሚበርሩ ወፎችም፣
11የምድር ነገሥታትና ሕዝቦች ሁሉ፣
መሳፍንትና የምድር ገዦች ሁሉ፣
12ወጣት ወንዶችና ደናግል፣
አረጋውያንና ልጆች ያመስግኑት።
13ስሙ ብቻውን ከፍ ያለ ነውና፣
ክብሩም ከምድርና ከሰማይ በላይ ነውና፣
እነዚህ ሁሉ የእግዚአብሔርን ስም ያመስግኑ።
14እርሱ ለሕዝቡ ቀንድን#148፥14 ቀንድ የጥንካሬ ትእምርት ሲሆን፣ ንጉሥን ያመለክታል። አስነሥቷል፤
ለቅዱሳኑ ሁሉ ምስጋና፣
እጅግ ቅርቡ ለሆነው ሕዝቡ፣ ለእስራኤል ልጆች።
ሃሌ ሉያ።
Currently Selected:
መዝሙር 148: NASV
Highlight
Share
Compare
Copy
Want to have your highlights saved across all your devices? Sign up or sign in
መጽሐፍ ቅዱስ፣ አዲሱ መደበኛ ትርጕም™
የቅጂ መብት © 2001, 2024 በBiblica, Inc.
በፈቃድ የሚወሰድ። በዓለም ዐቀፍ ባለቤትነቱ።
The Holy Bible, New Amharic Standard Version™
Copyright © 2001, 2024 by Biblica, Inc.
Used with permission. All rights reserved worldwide.