YouVersion Logo
Search Icon

መዝሙር 149

149
መዝሙር 149
የድል መዝሙር
1ሃሌ ሉያ።#149፥1 አንዳንዶች ከ9 ጭምር እግዚአብሔር ይመስገን ይላሉ።
ለእግዚአብሔር አዲስ ቅኔ ተቀኙ፤
ምስጋናውንም በቅዱሳን ጉባኤ ዘምሩ።
2እስራኤል በፈጣሪው ደስ ይበለው፤
የጽዮንም ልጆች በንጉሣቸው ሐሤት ያድርጉ።
3ስሙን በሽብሸባ ያመስግኑ፤ በከበሮና በመሰንቆ ይዘምሩለት።
4 እግዚአብሔር በሕዝቡ ደስ ይለዋልና፤
የዋሃንንም በማዳኑ ውበት ያጐናጽፋል።
5ቅዱሳን በዚህ ክብር ይጓደዱ፤
በመኝታቸውም ላይ እልል እያሉ ይዘምሩ።
6የአምላክ ውዳሴ በአንደበታቸው፣
ባለ ሁለት ልሳን ሰይፍም በእጃቸው ይሁን፤
7በዚህ ሕዝቦችን ይበቀላሉ፤
ሰዎችንም ይቀጣሉ፤
8ነገሥታታቸውን በሰንሰለት፣
መኳንንታቸውንም በእግር ብረት ያስራሉ፤
9ይህም በእነርሱ ላይ የተጻፈውን ፍርድ ለመፈጸም ነው።
ለቅዱሳኑም ሁሉ ይህች ክብር ናት።
ሃሌ ሉያ።

Currently Selected:

መዝሙር 149: NASV

Highlight

Share

Copy

None

Want to have your highlights saved across all your devices? Sign up or sign in

YouVersion uses cookies to personalize your experience. By using our website, you accept our use of cookies as described in our Privacy Policy