YouVersion Logo
Search Icon

መዝሙር 120

120
መዝሙር 120
የሰላም ፀሮች
መዝሙረ መዓርግ።
1በተጨነቅሁ ጊዜ ወደ እግዚአብሔር ተጣራሁ፤
እርሱም መለሰልኝ።
2 እግዚአብሔር ሆይ፤ ከሐሰተኛ ከንፈር፣
ከአታላይ ምላስም አድነኝ።
3ሐሰተኛ አንደበት ሆይ፤ ምን ይከፈልህ?
ከዚህስ የባሰ ምን ይደረግብህ?
4በተሳለ የጦረኛ ቀስት፣
በግራር ከሰል ፍም ይቀጣሃል።
5በሜሼክ እኖራለሁና፣ በቄዳር ድንኳኖች መካከል እቀመጣለሁና ወዮልኝ!
6ሰላምን በሚጠሉ መካከል፣
ነፍሴ እጅግ ብዙ ጊዜ ኖረች።
7እኔ ሰላም ፈላጊ ነኝ፤
እነርሱ ግን በተናገርሁ ጊዜ ጠብ ይሻሉ።

Currently Selected:

መዝሙር 120: NASV

Highlight

Share

Copy

None

Want to have your highlights saved across all your devices? Sign up or sign in

YouVersion uses cookies to personalize your experience. By using our website, you accept our use of cookies as described in our Privacy Policy