YouVersion Logo
Search Icon

መዝሙር 121

121
መዝሙር 121
የእስራኤል ጠባቂ
መዝሙረ መዓርግ።
1ዐይኖቼን ወደ ተራሮች አነሣሁ፤
ረድኤቴ ከወዴት ይመጣል?
2ረድኤቴ ሰማይንና ምድርን ከፈጠረ፣
ከእግዚአብሔር ዘንድ ይመጣል።
3እግርህ እንዲሸራተት አይፈቅድም፤
የሚጠብቅህም አይተኛም።
4እነሆ፤ እስራኤልን የሚጠብቅ አይተኛም፤ አያንቀላፋምም።
5 እግዚአብሔር ይጠብቅሃል፤
እግዚአብሔር በቀኝህ በኩል ይከልልሃል።
6ፀሓይ በቀን አያቃጥልህም፤
ጨረቃም በሌሊት ጕዳት አታመጣብህም።
7 እግዚአብሔር ከክፉ ሁሉ ይጠብቅሃል፤
ነፍስህንም ይንከባከባታል።
8 እግዚአብሔር ከአሁን ጀምሮ እስከ ዘላለም፣
መውጣትህንና መግባትህን ይጠብቃል።

Currently Selected:

መዝሙር 121: NASV

Highlight

Share

Copy

None

Want to have your highlights saved across all your devices? Sign up or sign in

YouVersion uses cookies to personalize your experience. By using our website, you accept our use of cookies as described in our Privacy Policy