1
የዮሐንስ ወንጌል 6:35
አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም
አማ05
ኢየሱስም እንዲህ አላቸው፦ “የሕይወት እንጀራ እኔ ነኝ፤ ወደ እኔ የሚመጣ ፈጽሞ አይራብም፤ በእኔ የሚያምን ፈጽሞ አይጠማም፤
So sánh
Khám phá የዮሐንስ ወንጌል 6:35
2
የዮሐንስ ወንጌል 6:63
ሕይወትን የሚሰጥ የእግዚአብሔር መንፈስ ነው፤ የሰው ኀይል ግን ለምንም አይጠቅምም፤ እኔ ለእናንተ የተናገርኩት ቃል መንፈስ ነው፤ ሕይወትም ነው፤
Khám phá የዮሐንስ ወንጌል 6:63
3
የዮሐንስ ወንጌል 6:27
ለሚጠፋ ምግብ አትሥሩ፤ ይልቅስ እግዚአብሔር አብ የማረጋገጫ ማኅተም ስለ አተመው የሰው ልጅ ለሚሰጣችሁ፥ የዘለዓለም ሕይወት ለሚሆነው ምግብ ሥሩ።”
Khám phá የዮሐንስ ወንጌል 6:27
4
የዮሐንስ ወንጌል 6:40
አዎ! የአባቴ ፈቃድ ወልድን የሚያይና በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘለዓለም ሕይወት እንዲያገኝ ነው፤ እኔም በመጨረሻው ቀን ከሞት አስነሣዋለሁ።”
Khám phá የዮሐንስ ወንጌል 6:40
5
የዮሐንስ ወንጌል 6:29
ኢየሱስም “የእግዚአብሔር ሥራማ እግዚአብሔር በላከው ማመን ነው” ሲል መለሰላቸው።
Khám phá የዮሐንስ ወንጌል 6:29
6
የዮሐንስ ወንጌል 6:37
አብ የሚሰጠኝ ሁሉ ወደ እኔ ይመጣል፤ ወደ እኔ የሚመጣውንም ፈጽሞ ወደ ውጪ አላባርረውም።
Khám phá የዮሐንስ ወንጌል 6:37
7
የዮሐንስ ወንጌል 6:68
በዚህ ጊዜ ስምዖን ጴጥሮስ እንዲህ ሲል መለሰ፦ “ጌታ ሆይ! ወደ ማን እንሄዳለን? አንተ የዘለዓለም ሕይወት ቃል አለህ።
Khám phá የዮሐንስ ወንጌል 6:68
8
የዮሐንስ ወንጌል 6:51
ከሰማይ የወረደው ሕይወትን የሚሰጥ እንጀራ እኔ ነኝ፤ ከዚህ እንጀራ የሚበላ ሁሉ ለዘለዓለም ይኖራል፤ ለዓለም ሕይወት እንዲሆን እኔ የምሰጠው እንጀራ ሥጋዬ ነው።”
Khám phá የዮሐንስ ወንጌል 6:51
9
የዮሐንስ ወንጌል 6:44
የላከኝ አብ የሳበው ካልሆነ በቀር ወደ እኔ መምጣት የሚችል ማንም የለም፤ ወደ እኔ የሚመጣውንም በመጨረሻ ቀን ከሞት አስነሣዋለሁ።
Khám phá የዮሐንስ ወንጌል 6:44
10
የዮሐንስ ወንጌል 6:33
የእግዚአብሔር እንጀራ ከሰማይ የሚወርድና ለዓለም ሕይወትን የሚሰጥ ነው።”
Khám phá የዮሐንስ ወንጌል 6:33
11
የዮሐንስ ወንጌል 6:48
እኔ የሕይወት እንጀራ ነኝ፤
Khám phá የዮሐንስ ወንጌል 6:48
12
የዮሐንስ ወንጌል 6:11-12
ከዚህ በኋላ ኢየሱስ እንጀራውን አንሥቶ ምስጋና ካቀረበ በኋላ ለተቀመጡት ሰዎች ዐደላቸው። እንዲሁም ዓሣዎቹን አከፋፈላቸው፤ ሁሉም የሚያስፈልጋቸውን ያኽል አገኙ። ሁሉም በልተው ከጠገቡ በኋላ ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱን፥ “አንድም ነገር እንዳይባክን የተረፈውንም ፍርፋሪ ሰብስቡ” አላቸው።
Khám phá የዮሐንስ ወንጌል 6:11-12
13
የዮሐንስ ወንጌል 6:19-20
ደቀ መዛሙርቱ አምስት ወይም ስድስት ኪሎ ሜትር ያኽል እየቀዘፉ ከተጓዙ በኋላ ኢየሱስ በባሕሩ ላይ እየተራመደ ወደ ጀልባዋ ሲቀርብ አይተው ፈሩ። እርሱ ግን “እኔ ነኝ! አትፍሩ!” አላቸው።
Khám phá የዮሐንስ ወንጌል 6:19-20
Trang chủ
Kinh Thánh
Kế hoạch
Video