Haggai: ቀጣዩ ምን ይሆን?Sample

እግዚአብሔርን ማስቀደም
ምናልባት ሕይወት እንቆቅልሽ በሆነ ወይም በጥፋት መንገድ አጨልሞብህ ይሆናል፣ በዚህም የቀረህ ቀጣዩስ ምንድነው ብለህ መጠየቅ ይሆን ይሆናል። ሁሉም ሰው እንደወትሮው በተስፋ መቁረጥ ውስጥ ያለ ይመስለዋል፤ ምናልባትም ለአንተ ህይወት ቀደም ሲል እንደነበረው ላይሆንህ ይችላል፡፡ ምን ሊሆን እንዳለም እርግጠኛ አይደለህም፡፡ የት እንደገና መገንባት መጀመር እንዳለበትም እርግጠኛ ልትሆን አትችልም፡፡ ምናልባት ብቻህን ቀርተህ ሊሆን ይችላል፣ በሀዘን ተመተህ ወይም የገንዘብ ክስረት ገጥሞህ ሊሆን ይችላል፤ እናም ቀጣዩ ምን ይሆን ወደሚለው ለመሄድ እምነት ያስፈልጋል፡፡
ምናልባት ሕይወት እንቆቅልሽ በሆነ ወይም በጥፋት መንገድ አጨልሞብህ ይሆናል፣ በዚህም የቀረህ ቀጣዩስ ምንድነው ብለህ መጠየቅ ይሆን ይሆናል። ሁሉም ሰው እንደወትሮው በተስፋ መቁረጥ ውስጥ ያለ ይመስለዋል፤ ምናልባትም ለአንተ ህይወት ቀደም ሲል እንደነበረው ላይሆንህ ይችላል፡፡ ምን ሊሆን እንዳለም እርግጠኛ አይደለህም፡፡ የት እንደገና መገንባት መጀመር እንዳለበትም እርግጠኛ ልትሆን አትችልም፡፡ ምናልባት ብቻህን ቀርተህ ሊሆን ይችላል፣ በሀዘን ተመተህ ወይም የገንዘብ ክስረት ገጥሞህ ሊሆን ይችላል፤ እናም ቀጣዩ ምን ይሆን ወደሚለው ለመሄድ እምነት ያስፈልጋል፡፡
በሐጌ ምዕራፍ 1 ላይ ብቻ ህዝቡ ልባቸውን በምን ላይ እንደጣሉ ለማንፀባረቅ አግዚአብሔር ሁለት ጊዜ ያህል “መንገዳችሁን ተመልከቱ!” እያለ ሲጠይቃቸው እናያለን፡፡ እኛም ልክ እንደ እስራኤላውያኑ በእጅጉ ልናስቀድም ከሚገባን ነገር ፈቀቅ ብለን የግል ፍላጎታችን ላይ እያተኮርን እንገኛለን፡፡ እስራኤላውያን የገዛ ፈቃዳቸውን ኑሮ በመኖር ወጥመድ ተይዘው ወደቁ፤ በዚህም እግዚአብሔርን ተዉ! እግዚአብሔርን የህይወትህ ማዕከል ለማድረግ የምታደርገው ጦርነት በህይወት ዘመንህ ከምታደርጋቸው የትኛውም ጦርነት ዋናና ወሳኙ ነው፤ ይህ ምንም እንኳን ወደ ዘላለም ጉዞ እያቀናህ ስትሄድ የሚገጥምህ ተግዳሮት ቢሆንም ልትጋደልለት የሚገባህ ጦርነት ነው።
ሐጌ ጀምሮ የሚያበቃው የእግዚአብሔር ኃይልና ታማኝነት ስላለው ውጤት በማሳየት ነው። እግዚአብሔር በህዝቡ መካከል በመኖር ጦርነቱን ተቀላቀለ ስለዚህም የእውነት ሊኖሩ ቻሉ፡፡ ሁኔታዎችህን አልፎ እርሱ በአንተ ትግል ውስጥም ይገባል፡፡ እግዚአብሔር እንድትሆን ወይም እንድትሠራ ለሚጠራህ ለማንኛውም ነገር የሰጠኸው ታማኝ ምላሽ አንተ ያለ እርሱ ፈፅሞ ልትጀምረው፣ ልታስቀጥለው ወይም ልትፈፅመው የምትችለው ነገር አይደለም። ደግነቱ አንተ የእርሱ ልጅ እንደሆንህ ለማስታወስና አንተን ወደ እርሱ ህብረት ለመጥራት አሁናዊ ሁኔታዎችህን ይጠቀማል።
ስለ ህዝቡ ታማኝነትና መታዘዝ እግዚአብሔር ቂሮስን አስነስቶ፤ ከምርኮ ነፃ አውጥቶ ወደ ምድራቸው እንዲገቡ መንገድን ጠርጓል፡፡ የፈረሰውን እንደገና የሚነገቡበትንም ግብዓት አቅርቧል፡፡ እግዚአብሔር አንተ እንዴት እርሱን ስታስቀድም የሚያዘጋጀውን ተመልከት፡፡ ስላጣኸው ነገር እያዘንህ ካለህ፣ ስላልተረጋገጠው ነገህ እየፈራህ ካለህ፣ ዛሬ ላይ ባለው ጫናዎች እንደተዋጥክ እየተሰማህ ካለህ፣ አንድ መጠየቅ ያለብህ ጥያቄ እንዳለህ እወቅ እርሱም “ቀጣዩ ምንድነው?” መልሱም እግዚአብሔርን ማስቀደም ነው፡፡ በእያንዳንዷ ቅፅበት ኢየሱስ መሄጃህ እና መደላደልህ መሆኑን እወቅ፡፡ እርሱ ከአንተ ጋር ነው፤ እርሱ ለአንተ ነው፤ እንዲሁም ታማኝነቱ መቼም አያልቅም፡፡
Scripture
About this Plan

ነገህን እየፈራህ ከሆነ ይህ የአምስት ቀናት እቅድ ለአንተ ነው፡፡ ምናልባት ልትቋቋመው የማትችለው አስቸጋሪ ሁኔታ ገጥሞህ ይሆናል፤ ነገር ግን በአንድ ነገር እርግጠኛ ሆነህ ኑር ይኸውም በአንተ ሕይወት የመጨረሻው ቃል ያለው እግዚአብሔር ነው፡፡ አግዚአብሐርን ማስቀደም፣ ህወትህን ከዓላማው ጋር ማጣጣም፤ በሚያጠነክርህና ቀጣዩ ምን እንደሆነ በሚያስቀጥልህ እውነት ላይ ማረፍን ተማር፡፡
More
Related Plans

Conversation Starters - Film + Faith - Forgiveness, Mentors, Tornadoes & More

Finding Strength in Stillness

EquipHer Vol. 24: "Who’s Economy Are You Working For?"

Film + Faith - Parents, Family and Marriage

Discover God’s Will for Your Life

Time Reset for Christian Moms

Live Well | God's Plan for Your Wellbeing

Slaying Giants Before They Grow

Collide
