BibleProject | የዘወረደ ምልከታዎችSample

ኢየሱስ ከብሉይ ኪዳን ህጎች መካከል ከሁሉ የሚበልጠው ህግ የቱ እንደሆነ በተጠየቀ ጊዜ መልስ የሰጠው ሼማ በመባል ከሚታወቀው ጥንታዊ ጸሎት በመጥቀስ ነው፦ "እግዚአብሔር አምላክህን በፍጹም ልብህ ውደድ።" ይህ ብቻ ግን አይደለም። ኢየሱስ በፍጥነት ሌላ የብሉይ ኪዳን ትዕዛዝ ከሁሉ እንደሚበልጥ ጨምሮ ተናግሯል፦ "ባልንጀራህን እንደራስህ ውደድ።" ስለዚህ ከሁሉ የሚበልጠው ህግ የቱ ነው? ለኢየሱስ ሁለቱም ወሳኝ ትዕዛዛት ናቸው፤ ምክንያቱም ያለሁለተኛው ትዕዛዝ የመጀመሪያውን ትዕዛዝ ማክበር አይችልም። አይለያዩም። አንድ ሰው ለእግዚአብሔር ያለውን ፍቅር የሚገለጠው ለሌሎች ባለው ፍቅር ነው።
ያንብቡ፦
ማርቆስ 12÷29-31፣ ዘዳግም 6÷5፣ ዘሌዋውያን 19÷18
ምልከታዎን ያስፍሩ፡
ኢየሱስ ከብሉይ ኪዳን ከጠቀሰ በኋላ ለሚናገረው ነገር ትኩረት ይስጡ። ንግግሩን ሲያስተውሉ የተፈጠረብዎት ጥያቄዎች፣ ሀሳቦች ወይም ስሜቶች ምንድን ናቸው?
ከዘዳግምና ዘሌዋውያን የተወሰዱትን ምንባቦች ይከልሱ። ምን ያስተውላሉ? ዛሬ ይህ በእርስዎ ላይ ምን ተጽዕኖ ያሳድራል?
ምልከታዎን ከልብ ወደመነጨ ጸሎት ይቀይሩት።
About this Plan

ባይብል ፕሮጀክት የዘወረደ ተከታታይ ትምህርቶችን ያዘጋጀው ግለሰቦች፣ ቡድኖች እንዲሁም ቤተሰቦች ዘወረደን፣ ማለትም የኢየሱስን ወደ ምድር መምጣት እንዲያከብሩ ለማነሳሳት ነው። ተስፋ፣ ሰላም፣ ሀሴት እና ፍቅር መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትርጉማቸው ምን እንደሚመስል ተሳታፊዎች እንዲያጤኑ ለማገዝ እንዲጠቅም፣ ይህ የአራት ሳምንት የጥናት እቅድ የአኒሜሽን ቪዲዮዎችን፣ አጫጭር ማጠቃለያዎችን እና ሃሳብ ጫሪ ጥያቄዎችን አካቷል። እነዚህ አራት መንፈሳዊ እሴቶች እንዴት በኢየሱስ በኩል ወደ አለም እንደመጡ ለመረዳት፣ ይህን የጥናት እቅድ ይምረጡ።
More
Related Plans

Gospel-Based Conversations to Have With Your Preteen

Who Am I, Really? Discovering the You God Had in Mind

Reimagine Influence Through the Life of Lydia

The Bible in a Month

Positive and Encouraging Thoughts for Women: A 5-Day Devotional From K-LOVE

Simon Peter's Journey: 'Grace in Failure' (Part 1)

The Holy Spirit: God Among Us

Sharing Your Faith in the Workplace

Never Alone
