ኦሪት ዘፍጥረት መግቢያ

መግቢያ
ኦሪት ዘፍጥረት ስለ ዓለማት አፈጣጠር፥ ስለ ሰው ዘር አመጣጥ፥ ስለ ኃጢአትና የሥቃይ ኑሮ አጀማመርና እግዚአብሔር ከሰው ዘር ጋር ስለ አለው ግንኙነት ይናገራል፤ ኦሪት ዘፍጥረት በሁለት ዋና ዋና ክፍሎች ሊመደብ ይችላል፦
1. ከምዕራፍ 1 እስከ 11 ስለ ዓለም አፈጣጠርና ስለ ሰው ዘር ቅድመ ታሪክ ይናገራል፤ የአዳምና የሔዋን፥ የቃየልና የአቤል፥ የኖኅና የጥፋት ውሃ፥ እንዲሁም የባቢሎን ግንብ ታሪክ የሚገኘው በዚህኛው ክፍል ነው።
2. ከምዕራፍ 12 እስከ 50 ይህ ክፍል ስለ እስራኤላውያን ቅድመ አባቶች ታሪክ ይናገራል፤ ከእነርሱም መካከል የመጀመሪያው በእምነቱና ለእግዚአብሔር በነበረው ታዛዥነት ታዋቂ የነበረው አብርሃም ነው፤ ከዚያም የልጁ የይስሐቅ፥ የልጁም ልጅ የነበረው የያዕቆብና የዐሥራ ሁለቱ የያዕቆብ ልጆች ታሪክ ይከተላል፤ እነዚህም ዐሥራ ሁለቱ የያዕቆብ ልጆች፥ ዐሥራ ሁለቱን የእስራኤል ነገዶች የመሠረቱ ናቸው፤ ከእነዚህም ዐሥራ ሁለቱ የእስራኤል ልጆች መካከል በተለይ ዮሴፍ ላይ፥ እንዲሁም፥ ያዕቆብንና የቀሩት ልጆቹን ከነቤተሰባቸው ወደ ግብጽ ባመጣው ሁኔታ ላይ ያተኲራል።
ምንም እንኳ ይህ መጽሐፍ ስለ ሕዝቦች ታሪክ የሚናገር ቢሆን ከሁሉ በላይ የሚተርከው እግዚአብሔር ስላደረገው ሥራ ነው፤ እግዚአብሔር ዓለማትን የመፍጠሩን ታሪክ መናገር ይጀምርና እግዚአብሔር ለሕዝቡ ማሰቡን እንደማያቋርጥ የሚያመለክተውን ተስፋ በመግለጥ ይጨርሳል፤ በመጽሐፉ ውስጥ ከዳር እስከ ዳር ዋናው ባለ ታሪክ ስሕተት በሚፈጽሙት ላይ ፍርድና ቅጣት የሚያስተላልፈው፥ ሕዝቡን የሚመራውና የሚረዳው፥ የታሪካቸውንም ሂደት የሚያስተካክለው ራሱ እግዚአብሔር ነው። ይህ ጥንታዊ መጽሐፍ የተጻፈው የሕዝቦችን እምነት ለማስፈርና ያንንም እምነት ሕያው ሆኖ እንዲኖር ለማድረግ ነው።
አጠቃላይ የመጽሐፉ ይዘት
ሀ. ፍጥረት 1፥1—2፥25
ለ. የኃጢአትና የችግር አጀማመር 3፥1-24
ሐ. ከአዳም እስከ ኖኅ 4፥1—5፥32
መ. ኖኅና የጥፋት ውሃ 6፥1—10፥32
ሠ. የባቢሎን ግንብ 11፥1-9
ረ. ከሴም እስከ አብርሃም 11፥10-32
ሰ. አባቶች አብርሃም፥ ይስሐቅ፥ ያዕቆብ 12፥1—35፥29
ሸ. የኤሳው ትውልድ 36፥1-43
ቀ. ዮሴፍና ወንድሞቹ 37፥1—45፥28
በ. እስራኤላውያን በግብጽ 46፥1—50፥26

ទើបបានជ្រើសរើសហើយ៖

ኦሪት ዘፍጥረት መግቢያ: አማ05

គំនូស​ចំណាំ

ចែក​រំលែក

ចម្លង

None

ចង់ឱ្យគំនូសពណ៌ដែលបានរក្សាទុករបស់អ្នក មាននៅលើគ្រប់ឧបករណ៍ទាំងអស់មែនទេ? ចុះឈ្មោះប្រើ ឬចុះឈ្មោះចូល

YouVersion ប្រើប្រាស់សំណល់ទិន្នន័យ (cookies) ដើម្បីកំណត់បទពិសោធន៍តម្រូវសម្រាប់អ្នក។ ដោយការប្រើប្រាស់គេហទំព័ររបស់យើងខ្ញុំ នោះអ្នកយល់ព្រមលើការប្រើប្រាស់សំណល់ទិន្នន័យរបស់យើងខ្ញុំ ដូចបានពណ៌នានៅក្នុង គោលការណ៍ច្បាប់ឯកជន របស់យើងខ្ញុំ