1
ኦሪት ዘፍጥረት 50:20
አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም
አማ05
በእርግጥ እናንተ ክፉ ነገር መክራችሁብኝ ነበር፤ እግዚአብሔር ግን ወደ መልካም ነገር ለወጠው፤ ይህንንም ያደረገው አሁን በሕይወት ያሉትን የብዙ ሰዎችን ሕይወት ለማትረፍ ብሎ ነው።
ប្រៀបធៀប
រុករក ኦሪት ዘፍጥረት 50:20
2
ኦሪት ዘፍጥረት 50:19
ነገር ግን ዮሴፍ እንዲህ አላቸው፤ “አይዞአችሁ አትፍሩ፤ እኔ በእግዚአብሔር ምትክ የምሆን አይደለሁም፤
រុករក ኦሪት ዘፍጥረት 50:19
3
ኦሪት ዘፍጥረት 50:21
ምንም የሚያስፈራችሁ ነገር የለም፤ እኔ እናንተንና ልጆቻችሁን እመግባችኋለሁ።” በዚህም ዐይነት በመልካም ንግግር በማጽናናት አረጋጋቸው።
រុករក ኦሪት ዘፍጥረት 50:21
4
ኦሪት ዘፍጥረት 50:17
‘ወንድሞችህ በበደሉህ ጊዜ ያደረሱብህን ጒዳት ሁሉ አትቊጠርባቸው ብሎሃል’ ብለን እንድንነግርህ አዞናል፤ ስለዚህ እኛ የአባትህ አምላክ አገልጋዮች ያደረስንብህን በደል ሁሉ ይቅር እንድትለን እንለምንሃለን።” ዮሴፍ ይህን በሰማ ጊዜ አለቀሰ።
រុករក ኦሪት ዘፍጥረት 50:17
5
ኦሪት ዘፍጥረት 50:24
ከዚህ በኋላ ዮሴፍ ወንድሞቹን እንዲህ አላቸው፤ “እነሆ እኔ የምሞትበት ጊዜ ተቃርቦአል፤ እናንተን ግን እግዚአብሔር በረድኤት ይጐበኛችኋል፤ ከዚህም አገር አውጥቶ ለአብርሃም፥ ለይስሐቅና ለያዕቆብ ለመስጠት በመሐላ ቃል ወደ ገባላቸው ምድር ይመልሳችኋል።
រុករក ኦሪት ዘፍጥረት 50:24
6
ኦሪት ዘፍጥረት 50:25
እግዚአብሔር በሚጐበኛችሁና ወደዚያች ምድር በሚመልሳችሁ ጊዜ ዐፅሜን ከዚህ ይዛችሁ የምትወጡ መሆናችሁን በማረጋገጥ ቃል ግቡልኝ” ብሎ አስማላቸው።
រុករក ኦሪት ዘፍጥረት 50:25
7
ኦሪት ዘፍጥረት 50:26
ዮሴፍም ዕድሜው መቶ ዐሥር ዓመት ሲሞላው ሞተ፤ አስከሬኑንም በሽቶ አሽተው በማድረቅ በግብጽ ምድር በሣጥን ውስጥ አኖሩት።
រុករក ኦሪት ዘፍጥረት 50:26
គេហ៍
ព្រះគម្ពីរ
គម្រោងអាន
វីដេអូ