መዝሙር 110
110
መዝሙር 110
የዳዊት መዝሙር።
1 እግዚአብሔር ጌታዬን፣
“ጠላቶችህን ለእግርህ መረገጫ፣
እስከማደርግልህ ድረስ፣
በቀኜ ተቀመጥ” አለው።
2 እግዚአብሔር ብርቱ በትርህን ከጽዮን ወደ ውጭ ይሰድዳል፤
“አንተም በጠላቶችህ መካከል ሆነህ ትገዛለህ።”
3ለጦርነት በምትወጣበት ቀን፣
ሰራዊትህ በገዛ ፈቃዱ በጐንህ ይቆማል፤
ከንጋት ማሕፀን፣
በቅዱስ ግርማ ደምቀህ፣
የጕልማሳነትህን ልምላሜ#110፥3 ወይም ጕልማሶችህ እንደ ንጋት ወዳንተ ይመጣሉ ማለት ነው። እንደ ጠል ትቀበላለህ።
4“እንደ መልከ ጼዴቅ ሥርዐት፤
አንተ ለዘላለም ካህን ነህ” ብሎ፣
እግዚአብሔር ምሏል፤
እርሱ ሐሳቡን አይለውጥም።
5ጌታ በቀኝህ ነው፤
በቍጣውም ቀን ነገሥታትን ያደቅቃቸዋል።
6በሕዝቦች መካከል ይፈርዳል፤
በየአገሩ ያሉትንም ራሶች ከስክሶ ሬሳ በሬሳ ያደርጋቸዋል።
7መንገድ#110፥7 ወይም ሥልጣን ለመስጠት ኀይል ያለው ሥልጣን ላይ ያስቀምጠዋል ዳር ካለች ፈሳሽ ውሃ ይጠጣል፤
ስለዚህ ራሱን ቀና ያደርጋል።
Currently Selected:
መዝሙር 110: NASV
Highlight
Copy
Compare
Share
Want to have your highlights saved across all your devices? Sign up or sign in
መጽሐፍ ቅዱስ፣ አዲሱ መደበኛ ትርጕም™
የቅጂ መብት © 2001, 2024 በBiblica, Inc.
በፈቃድ የሚወሰድ። በዓለም ዐቀፍ ባለቤትነቱ።
The Holy Bible, New Amharic Standard Version™
Copyright © 2001, 2024 by Biblica, Inc.
Used with permission. All rights reserved worldwide.