1
መጽሐፈ መክብብ 11:9
አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም
አማ05
ወጣት ሆይ! ወጣትነት እጅግ ግሩም ስለ ሆነ በወጣትነትህ ዘመን ደስ ይበልህ፤ በልብህም ሐሤት አድርግ፤ ዐይንህ የሚያየውንና ልብህ የሚመኘውን ሁሉ ፈጽም፤ ሆኖም ስለዚህ ነገር ሁሉ እግዚአብሔር ወደ ፍርድ እንደሚያመጣህ ዕወቅ።
Compare
Explore መጽሐፈ መክብብ 11:9
2
መጽሐፈ መክብብ 11:10
የወጣትነትና የብርቱ ጐልማሳነት ጊዜ ቶሎ ስለሚያልፍ ሐዘንን ከልብህ፥ ጭንቀትንም ከአእምሮህ አስወግድ።
Explore መጽሐፈ መክብብ 11:10
3
መጽሐፈ መክብብ 11:4
ነፋስን የሚጠብቅ አይዘራም፤ ደመናን የሚመለከት አያጭድም።
Explore መጽሐፈ መክብብ 11:4
4
መጽሐፈ መክብብ 11:5
የነፋስን አካሄድና የሰውም ሕይወት አፈጣጠር በእናቱ ማሕፀን እንዴት እንደሚጀመር እንደማታውቅ የሁሉ ነገር ፈጣሪ እግዚአብሔር ሥራውን እንዴት እንደሚያከናውን ማወቅ አትችልም።
Explore መጽሐፈ መክብብ 11:5
5
መጽሐፈ መክብብ 11:6
ጧትም ሆነ ማታ ዘር መዝራትህን አታቋርጥ፤ ሁሉም ይበቅል ወይም አይበቅል እንደ ሆነ የትኛው አዘራር እንደሚሻል ለይተህ ማወቅ አይቻልህም።
Explore መጽሐፈ መክብብ 11:6
6
መጽሐፈ መክብብ 11:2
ወደ ፊት በዓለም ላይ ምን ዐይነት ክፉ ነገር እንደሚመጣ አታውቅም፤ ስለዚህ ያለህን ሀብት በሰባት ወይም በስምንት ቦታ ከፋፍለህ አኑር።
Explore መጽሐፈ መክብብ 11:2
Home
Bible
Plans
Videos