መከራንና ሥቃይን መቋቋም የሚቻለው እንዴት ነው?ናሙና

ከአምላክ ፊት ርቆ ከመኖር ይልቅ መከራን መቀበል ይሻላል።
"ሌሎች ሲነቅፉአችሁና ሲያሳድዱአችሁ በእኔም ምክንያት ክፉውን ሁሉ በውሸት ሲናገሩባችሁ ብፁዓን ናችሁ። ዋጋችሁ በሰማያት ታላቅ ነውና ደስ ይበላችሁ ሐሴትም አድርጉ ከእናንተ በፊት የነበሩትን ነቢያትን እንዲሁ አሳድደዋቸዋልና” ( ማቴዎስ 5:11-12 )።
የኢየሱስን እርምጃዎች ስንከተል እና ከእሱ ጋር ተስማምተን ስንኖር፣ የእግዚአብሔርን መገኘት ደስታ እናገኛለን። ከዚህም በላይ ኢየሱስ “የተባረክን” ብሎ የጠራን ሲሆን ለእርሱ ስንሰደድ ታላቅ ሽልማት እንደሚሰጠን ቃል ገብቷል።
ሐዋርያው ጴጥሮስ ስደትን ለማስወገድ ሞክሮ ነበር። ኢየሱስ ተይዞ ሲጠየቅ ጴጥሮስ ግን ካደው። የኢየሱስ ደቀ መዝሙር በመሆን እራሱን ለመያዝ በጣም ስለፈራ “ይህን ሰው” እንደማያውቀው ምሎ ነበር። አመለጠም፤ ነገር ግን ያደረገውን ባወቀ ጊዜ ምርር ብሎ አለቀሰ (ማቴ 26፡75)። አዎ ኢየሱስን መከተል ዋጋ ያስከፍላል። ለፅድቅ ስትል ብትሰደድ በጣም ከባድ ሊሆን ይችላል ነገር ግን መሸሽ ዘላቂ ደስታን አያመጣልህም። ከእግዚአብሔር መገኘት ውጭ መሆን ጨለማ ነው ያለው።
ጴጥሮስ ኢየሱስን ክዶ ነበር፣ ኢየሱስ ግን ይቅር ብሎት ሐዋርያ አድርጎ መልሶታል። በዚህ ጊዜ ጴጥሮስ አዲስ ደስታና ሰላም አገኘ። ጴጥሮስ ይህን የግል ተሞክሮ በአእምሮው ይዞ አንባቢዎቹን “ስለ ጽድቅ እንኳ መከራን ብትቀበሉ ብፁዓን ትሆናላችሁ። አትፍሩአቸው አትደንግጡም…” (1ኛ ጴጥሮስ 3፡14)
ስደት ቢኖርም በእግዚአብሔር ፊት ሰላምና ደስታ አለ።
ቅዱሳት መጻሕፍት
ስለዚህ እቅድ

ሐዋርያው ጳውሎስ ለአንባቢዎቹ “ወደ እግዚአብሔር መንግሥት በብዙ መከራ እንገባ ዘንድ ያስፈልገናል” (የሐዋርያት ሥራ 14:22) ይላል። የሐዋርያት ሥራን ማንበብ ወይም በዓለም ዙሪያ ካሉ ክርስቲያኖችን ምስክርነት መስማት፣ የዚህን ቃል እውነት አረጋግጠዋል። አማኞች ተቃውሞ እና ስደት ይደርስባቸዋል። ምናልባት እርሶም መከራ አጋጥሞት ይሆናል። በዚህ የንባብ እቅድ ውስጥ፣ ልናበረታታዎት እና በመከራን እንዴት መቋቋም እንደሚቻል ማስተማር እንፈልጋለን።
More
ይህንን እቅድ ስላቀረበልን GlobalRize ን ልናመሰግን እንወዳለን። ለበለጠ መረጃ፣እባክዎ የሚከተለውን ይጎብኙ፡ globalrize.org