ለዕለት ተዕለት ሕይወትዎ ተስፋSample

“እምቢ” ለማለት ትክክለኛው ጊዜ
እጅግ ከብዶኛልና ይህን ሁሉ ህዝብ ብቻዬን ልሸከም አልችልም፡፡ - ዘሁ 11፡14
በዘሁልቁ 11 ላይ በጭንቀት ውስጥ ስናልፍ ምን ልናደርግ እንደምንችል ሙሴ ምሳሌ ሰጥቶናል፡፡ እስራኤላዊያንን በምድረበዳ በሚመራ ወቅት ፤ አስራአንድ ቀን ብቻ መፍጀት የሚገባው ጉዞ አርባ አመት ሲወስድ ስለነበረው ጫና ያወራል!
ህዝቡ በድብርት ውስጥ እና ካሉበትሁኔታ የተነሳ በለቅሶ ውስጥ ነበሩ፡፡በቁጥር 14 ላይ ሙሴ እግዚአብሔርን “እጅግ ከብዶኛልና ይህን ሁሉ ህዝብ ብቻዬን ልሸከም አልችልም፡፡” ብሎ ይነግረዋል።
ልክ እንደሙሴ እኛም “ከአቅሜ በላይ ሆኖብኛል” ማለት እንችላለን፡፡አዎ መጽሀፍ ቅዱስ ፊሊጲሲዩስ 4፡13 ላይ ሲናገር ሀይልን በሚሰጠኝ በክርስቶስ ሁሉን እችላለሁ ይላል፡፡ነገር ግን ይሄ የሚያመለክተው የተለያዩ ችግሮች እና ሁኔታዎች ሲያጋጥሙን እግዚአብሔር በዚያ ውስጥ እንደሚረዳን ነው፡፡
ልክ የአምስት ልጆ እናት ሆና ሙሉጊዜ የምትሰራ፣ በቤተክርስቲያን ቦርድ ውስጥ የምታገለግል እና ሌሎችም ኃላፊነቶች ያሉባት ሴት አይነት በጣም ብዙ ኃላፊነቶችን ተቀብለን ከጥቅም ውጪ መሆን አለብን ማለት አይደለም፡፡
አንዳንዴ በቃ ከአቅም በላይ ይሆናል… እናም ደግሞ ይሄንን ማመን ምንም ችግር የለውም፡፡እግዚአብሔር በወሰነው መሰረት በህይወት ለመደሰት አንዳንድ ነገሮችን “እምቢ” ማለትም ችግር የለውም፡፡
እዚህ ጋር አንድ ነገር ልበል፡እኔ እና እናንተ እንደሌላው ሰው መሆን የለብንም ወይም ሌላ ሰው ጋር መፎካከር የለብንም፡፡እግዚአብሔር አንዳንድ ሰዎችን ብዙ ስራ እንዲሸከሙ አድርጎ ነው የፈጠራቸው ብዙ ሰዎች ግን በዚያ መንገድ አይደለም የተፈጠሩት፡፡
እያንዳንዳችን እግዚአብሔር የፈጠረንን ነው መሆን ያለብን፤ያንን ስለሆንን ደግሞ ይቅርታ መጠየቅ የለብንም፡፡እኛ እያንዳንዳችን በጭንቀት እና በጫና ራሳችንን ከማሳመም ይልቅ ህይወታችንን ተደስተን እንድንኖርበት እግዚአብሔር የመደበልንን ሚዛናዊ የሆነ ኃላፊነታችንን ማግኘት ይኖርብናል፡፡
ከአቅማችሁ በላይ ሲሆን እንደ ሙሴ ወደ እግዚአብሔር ሂዱ፡፡የተረጋጋ እና ጤናማ የሆነ የአኗኗር ዘይቤ እንዲኖራችሁ ይረዳችኋል፡፡
የጸሎት መጀመሪያ
እግዚአብሔር ሆይ፣አንዳንድ ጊዜ መረጋገት እና ተጨማሪ ኀላፊነትን ላለመቀበል “እምቢ” ማለት ይከብደኛል፡፡በአንተ ሰላም ውስጥ እንድኖር እና ህይወትን እንዳጣጥመው ለእኔ ከፈጠርከው ሚዛናዊ ኃላፊነት ጋር እንድኖር እርዳኝ፡፡
Scripture
About this Plan

ቀንዎን ከጆይስ ሜየር ተግባራዊ በሆነ የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ይጀምሩ። ይህ ዕለታዊ ማበረታቻ ተስፋ እንዲኖርዎ ፣ አዕምሮዎን ማደስ እንዲችሉ እንዲሁም በየቀኑ በዓላማ መኖር እንዲችሉ ያግዛል!
More
Related Plans

Workplace Wisdom: Communication

Christian Foundations 3 - Growth

Drawing Closer: An Everyday Guide for Lent

Ruth: A Story of Choices

Finding Strength in Stillness

EquipHer Vol. 26: "How to Break the Cycle of Self-Sabotage"

EquipHer Vol. 24: "Who’s Economy Are You Working For?"

Made New: Rewriting the Story of Rejection Through God's Truth

Discover God’s Will for Your Life
