መዝሙረ ዳዊት 77:10-20
መዝሙረ ዳዊት 77:10-20 አማ2000
የእግዚአብሔርን ኪዳን አልጠበቁምና፥ በሕጉም ለመሄድ እንቢ አሉ፤ ረድኤቱንና ያሳያቸውን ተአምራቱን ረሱ፥ በግብጽ ሀገርና በጣኔዎስ በረሃ በአባቶቻቸው ፊት የሠራውን ተአምራት። ባሕርን ከፍሎ አሳለፋቸው፤ ውኆችን እንደ ረዋት ውኃ አቆመ። ቀን በደመና መራቸው፥ ሌሊቱንም ሁሉ በእሳት ብርሃን። ዓለቱን በምድረ በዳ ሰነጠቀ፤ ከብዙ ጥልቅ እንደሚገኝ ያህል አጠጣቸው። ውኃንም እንደ ወንዞች አፈሰሰ። ውኃንም ከዓለት አፈለቀ፥ ነገር ግን እርሱን መበደልን እንደገና ደገሙ፥ ልዑልንም በምድረ በዳ አስመረሩት። ለነፍሳቸው መብልን ይፈልጉ ዘንድ፥ እግዚአብሔርን በልባቸው ፈተኑት። እግዚአብሔርን እንዲህ ብለው አሙት፦ “እግዚአብሔር በምድረ በዳ ማዕድን ያሰናዳ ዘንድ ዓለቱን ይመታ ዘንድ ውኃንም ያፈስ ዘንድ ይችላልን? እንጀራን መስጠትና ለሕዝቡስ ማዕድን መሥራት ይችላልን?”