YouVersion Logo
Search Icon

መዝሙረ ዳዊት 6

6
1ለመዘምራን አለቃ በበገናዎች ስለ ስምንተኛ፥ የዳዊት መዝሙር።
2 # መዝ. 38፥2። አቤቱ፥ በቁጣህ አትቅሠፈኝ፥
በመዓትህም አትገሥጸኝ።
3 # ኤር. 17፥14-15። ዝያለሁና አቤቱ፥ ማረኝ፥
አጥንቶቼ ታውከዋልና ፈውሰኝ።
4 # መዝ. 13፥2-3፤ 74፥10፤ 89፥47። ነፍሴም እጅግ ታወከች፥
አንተም አቤቱ፥ እስከ መቼ ድረስ ነው?
5አቤቱ፥ ተመለስ ነፍሴንም አድናት፥
ስለ ቸርነትህም አድነኝ።
6 # መዝ. 30፥10፤ 88፥11፤ 115፥17፤ ኢሳ. 38፥18። በሞት የሚያስታውስህ የለምና፥
በሲኦልም የሚያመሰግንህ ማን ነው?
7በመቃተቴ ደክሜአለሁ፥
ሌሊቱን ሁሉ አልጋዬን በእንባ አጥባለሁ፥
በዕንባዬም መኝታዬን አርሳለሁ።
8 # መዝ. 31፥10፤ 38፥11፤ 40፥13። ዓይኔ ከኀዘን ዕንባ የተነሣ ታወከች፥
ከጠላቶቼ ሁሉ የተነሣ ደከመች።
9 # መዝ. 119፥115፤ ማቴ. 7፥23፤ ሉቃ. 13፥27። ዓመፃን የምታደርጉ ሁሉ፥ ከእኔ ራቁ፥
ጌታ የልቅሶዬን ቃል ሰምቶአልና።
10ጌታ ልመናዬን ሰማኝ፥
ጌታ ጸሎቴን ተቀበለ።
11 # መዝ. 35፥4፤ 26፤ 40፥15፤ 71፥13። ጠላቶቼ ሁሉ ይፈሩ እጅግም ይጐስቁሉ፥
ወደ ኋላቸው ይመለሱ፥ በፍጥነትም ይፈሩ።

Highlight

Share

Copy

None

Want to have your highlights saved across all your devices? Sign up or sign in

Videos for መዝሙረ ዳዊት 6