መጽሐፈ መዝሙር 131
131
በእግዚአብሔር መታመን
1እግዚአብሔር ሆይ! ልቤ በኩራት የተወጠረ አይደለም፤
ዐይኖቼም ትዕቢተኞች አይደሉም፤
ስለ ታላላቅ ነገሮች ወይም ላስተውለው
ስለማልችለው ከባድ ነገር አልጨነቅም።
2አንድ ጡት የተወ ሕፃን በእናቱ ደረት ላይ እንደሚለጠፍ
እኔም ዝምተኛና ጸጥተኛ ሆንኩ።
3እስራኤል ሆይ! ከአሁን ጀምሮ እስከ ዘለዓለም
እግዚአብሔርን ተስፋ አድርግ!
Currently Selected:
መጽሐፈ መዝሙር 131: አማ05
Highlight
Share
Copy
Want to have your highlights saved across all your devices? Sign up or sign in
© The Bible Society of Ethiopia, 2005
© የኢትዮጵያ መጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር፥ 1997