YouVersion Logo
Search Icon

መዝሙር 92

92
መዝሙር 92
ጻድቅ ሰው ሲደሰት
በሰንበት ቀን የሚዘመር መዝሙር፤ ማሕሌት።
1 እግዚአብሔርን ማመስገን መልካም ነው፤
ልዑል ሆይ፤ ለስምህ መዘመር ጥሩ ነው፤
2ምሕረትህን በማለዳ፣
ታማኝነትህንም በሌሊት ማወጅ መልካም ነው፤
3ዐሥር አውታር ባለው በገና፣
በመሰንቆም ቅኝት ታጅቦ ማወጅ ጥሩ ነው።
4 እግዚአብሔር ሆይ፤ በሥራህ ስለ ተደሰትሁ፣
ስለ እጅህ ሥራ በደስታ እዘምራለሁ።
5 እግዚአብሔር ሆይ፤ ሥራህ እንዴት ታላቅ ነው!
ሐሳብህስ ምን ያህል ጥልቅ ነው!
6ደነዝ ሰው ይህን አያውቅም፤
ነኁላላም አያስተውለውም።
7ክፉዎች እንደ ሣር ቢበቅሉ፣
ክፉ አድራጊዎች ቢለመልሙ፣
ለዘላለሙ ይጠፋሉ፤
8 እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ ግን ለዘላለም ልዑል ነህ።
9ጠላቶችህ እግዚአብሔር ሆይ፤ ጠላቶችህ ይጠፋሉና፤
ክፉ አድራጊዎችም ሁሉ ይበተናሉ።
10የእኔን ቀንድ ግን እንደ አውራሪስ ቀንድ#92፥10 ጥንካሬን የሚያመለክት ነው። ከፍ ከፍ አደረግኸው፤
በለጋ ዘይትም አረሰረስኸኝ።
11ዐይኖቼ የባላንጦቼን ውድቀት አዩ፤
ጆሮዎቼም የክፉ ጠላቶቼን ድቅቀት ሰሙ።
12ጻድቃን እንደ ዘንባባ ይንሰራፋሉ፤
እንደ ሊባኖስ ዝግባም ይንዠረገጋሉ።
13 በእግዚአብሔር ቤት ተተክለዋል፤
በአምላካችንም አደባባይ ይንሰራፋሉ።
14ባረጁ ጊዜ እንኳ ያፈራሉ፤
እንደ ለመለሙና እንደ ጠነከሩም ይኖራሉ።
15እግዚአብሔር ትክክለኛ ነው፤
እርሱ ዐለቴ ነው፤ በእርሱ ዘንድ እንከን የለም” ይላሉ።

Currently Selected:

መዝሙር 92: NASV

Highlight

Share

Copy

None

Want to have your highlights saved across all your devices? Sign up or sign in

YouVersion uses cookies to personalize your experience. By using our website, you accept our use of cookies as described in our Privacy Policy