YouVersion Logo
Search Icon

መዝሙር 138

138
መዝሙር 138
የዳዊት መዝሙር።
1በፍጹም ልቤ አመሰግንሃለሁ፤
“በአማልክት” ፊት በመዝሙር አወድስሃለሁ።
2ወደ ቅዱስ መቅደስህ እሰግዳለሁ፤
ስለ ምሕረትህና ስለ ታማኝነትህ፣
ለስምህ ምስጋና አቀርባለሁ፤
ስምህንና ቃልህን፣
ከሁሉ በላይ ከፍ ከፍ አድርገሃልና።
3በጠራሁህ ቀን መልስ ሰጠኸኝ፤
ነፍሴን በማደፋፈርም ብርቱ አደረግኸኝ።
4 እግዚአብሔር ሆይ፤ የአፍህን ቃል በሰሙ ጊዜ፣
የምድር ነገሥታት ሁሉ ያመስግኑህ።
5 የእግዚአብሔር ክብር ታላቅ ነውና፣
ስለ እግዚአብሔር መንገድ ይዘምሩ።
6 እግዚአብሔር በከፍታ ስፍራ ቢሆንም፣ ዝቅ ያለውን ይመለከተዋል፤
ትዕቢተኛውን ከሩቅ ያውቀዋል።
7በመከራ መካከል ብሄድም፣
አንተ ሕይወቴን ትጠብቃታለህ፤
በጠላቶቼ ቍጣ ላይ እጅህን ትዘረጋለህ፤
በቀኝ እጅህም ታድነኛለህ።
8 እግዚአብሔር በእኔ ላይ ያለውን ዐላማ ይፈጽማል፤
እግዚአብሔር ሆይ፤ ምሕረትህ ለዘላለም ነው።
የእጅህንም ሥራ ቸል አትበል።

Currently Selected:

መዝሙር 138: NASV

Highlight

Share

Copy

None

Want to have your highlights saved across all your devices? Sign up or sign in

Video for መዝሙር 138