YouVersion Logo
Search Icon

መዝሙር 1

1
አንደኛ መጽሐፍ
ከመዝሙር 1–41
መዝሙር 1
1ብፁዕ ነው፣
በክፉዎች ምክር የማይሄድ፣
በኀጢአተኞች መንገድ የማይቆም፣
በፌዘኞችም ወንበር የማይቀመጥ፤
2ነገር ግን ደስ የሚሠኘው በእግዚአብሔር ሕግ ነው፤
ሕጉንም በቀንና በሌሊት ያሰላስለዋል።
3እርሱም በወራጅ ውሃ ዳር እንደ ተተከለች፣
ፍሬዋን በየወቅቱ እንደምትሰጥ፣
ቅጠሏም እንደማይጠወልግ ዛፍ ነው፤
የሚሠራውም ሁሉ ይከናወንለታል።
4ክፉዎች ግን እንዲህ አይደሉም፤
ነገር ግን ነፋስ ጠራርጎ እንደሚወስደው
ገለባ ናቸው።
5ስለዚህ ክፉዎች በፍርድ ፊት፣
ኀጢአተኞችም በጻድቃን ማኅበር መቆም አይችሉም።
6 እግዚአብሔር የጻድቃንን መንገድ ይጠብቃልና፤
የክፉዎች መንገድ ግን ትጠፋለች።

Currently Selected:

መዝሙር 1: NASV

Highlight

Share

Compare

Copy

None

Want to have your highlights saved across all your devices? Sign up or sign in