YouVersion Logo
Search Icon

ናሆም 1

1
1ስለ ነነዌ ጥፋት የተነገረ ንግር፤ የኤልቆሻዊው የናሆም የራእዩ መጽሐፍ ይህ ነው፤
በነነዌ ላይ የተገለጠ የእግዚአብሔር ቍጣ
2 እግዚአብሔር ቀናተኛና ተበቃይ አምላክ ነው፤
እግዚአብሔር የሚበቀል፣ በመዓትም የተሞላ ነው።
እግዚአብሔር ባላጋራዎቹን ይበቀላል፤
በጠላቶቹም ላይ ቍጣውን ያመጣል።
3 እግዚአብሔር ለቍጣ የዘገየ፣ በኀይሉም ታላቅ ነው፤
እግዚአብሔር በደለኛውን ሳይቀጣ አያልፍም፤
መንገዱ በዐውሎ ነፋስና በማዕበል ውስጥ ነው፤
ደመናም የእግሩ ትቢያ ነው።
4ባሕርን ይገሥጻል፤ ያደርቀዋልም፤
ወንዞችን ሁሉ ያደርቃል።
ባሳንና ቀርሜሎስ ጠውልገዋል፤
የሊባኖስም አበቦች ረግፈዋል።
5ተራሮች በፊቱ ታወኩ፤
ኰረብቶችም ቀለጡ።
ምድር በፊቱ፣
ዓለምና በውስጧ የሚኖሩት ሁሉ ተናወጡ።
6ቍጣውን ማን ሊቋቋም ይችላል?
ጽኑ ቍጣውንስ ማን ሊሸከም ይችላል?
መዓቱ እንደ እሳት ፈስሷል፤
ዐለቶችም በፊቱ ተሰነጣጥቀዋል።
7 እግዚአብሔር መልካም ነው፤
በጭንቅ ጊዜም መሸሸጊያ ነው።
ለሚታመኑበት ይጠነቀቅላቸዋል፤
8ነነዌን ግን፣
በሚያጥለቀልቅ ጐርፍ ያጠፋታል፤
ጠላቶቹንም ወደ ጨለማ ያሳድዳቸዋል።
9 በእግዚአብሔር ላይ ምንም ቢያሤሩ#1፥9 በእግዚአብሔር ላይ የምታሤሩት ምንድን ነው? የሚሉ አሉ።
እርሱ ያጠፋዋል፤
መከራም ዳግመኛ አይነሣም።
10በእሾኽ ይጠላለፋሉ፤
በወይን ጠጃቸውም ይሰክራሉ፤
እሳትም እንደ ገለባ#1፥10 የዕብራይስጡ ትርጕም በትክክል አይታወቅም። ይበላቸዋል።
11ነነዌ ሆይ፤ በእግዚአብሔር ላይ የሚያሤር፣
ክፋትንም የሚመክር፣
ከአንቺ ዘንድ ወጥቷል።
12 እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤
“ምንም ኀይለኞችና ብዙዎች ቢሆኑም፣
ይቈረጣሉ፤ ይጠፋሉም።
ይሁዳ ሆይ፤ ከዚህ በፊት ባስጨንቅህም፣
ከእንግዲህ አላስጨንቅህም።
13አሁንም ቀንበራቸውን ከዐንገትህ ላይ አንሥቼ እሰብራለሁ፤
የታሰርህበትንም ሰንሰለት በጥሼ እጥላለሁ።”
14አንቺ ነነዌ፤ እግዚአብሔር ስለ አንቺ እንዲህ ብሎ አዝዟል፤
“ስም የሚያስጠራ ትውልድ አይኖራችሁም፤
በአማልክታችሁ ቤት ያሉትን፣
የተቀረጹትን ምስሎችና ቀልጠው የተሠሩትን ጣዖታት እደመስሳለሁ፤
መቀበሪያህን እምስልሃለሁ፤
አንተ ክፉ ነህና።”
15እነሆ፤ የምሥራች የሚያመጣው፣
ሰላምን የሚያውጀው ሰው እግር፣
በተራሮች ላይ ነው፤
ይሁዳ ሆይ፤ በዓላትህን አክብር፤
ስእለትህንም ፈጽም፤
ከእንግዲህ ክፉዎች አይወርሩህም፤
እነርሱም ፈጽመው ይጠፋሉ።

Currently Selected:

ናሆም 1: NASV

Highlight

Share

Copy

None

Want to have your highlights saved across all your devices? Sign up or sign in

YouVersion uses cookies to personalize your experience. By using our website, you accept our use of cookies as described in our Privacy Policy