ዕዝራ 2
2
ወደ አገራቸው የተመለሱ ምርኮኞች ዝርዝር
2፥1-70 ተጓ ምብ – ነህ 7፥6-73
1የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነፆር ወደ ባቢሎን ማርኮ ከወሰዳቸው መካከል ከምርኮ ተመልሰው ወደ የራሳቸው ከተሞች፣ ወደ ይሁዳና ወደ ኢየሩሳሌም የመጡት የአገሩ ልጆች እነዚህ ናቸው፤ 2የመጡትም ከዘሩባቤል፣ ከኢያሱ፣ ከነህምያ፣ ከሠራያ፣ ከረዕላያ፣ ከመርዶክዮስ፣ ከበላሳን፣ ከመሴፋር፣ ከበጉዋይ፣ ከሬሁም፣ ከበዓና ጋር ነበር።
የተመለሱት የእስራኤል ሰዎች ዝርዝር የሚከተለው ነው፦
3የፋሮስ ዘሮች | 2,172 |
4የሰፋጥያስ ዘሮች | 372 |
5የኤራ ዘሮች | 775 |
6ከኢያሱና ከኢዮአብ ዘር የሆኑት የፈሐት ሞዓብ ዘሮች | 2,812 |
7የኤላም ዘሮች | 1,254 |
8የዛቱዕ ዘሮች | 945 |
9የዘካይ ዘሮች | 760 |
10የባኒ ዘሮች | 642 |
11የቤባይ ዘሮች | 623 |
12የዓዝጋድ ዘሮች | 1,222 |
13የአዶኒቃም ዘሮች | 666 |
14የበጉዋይ ዘሮች | 2,056 |
15የዓዲን ዘሮች | 454 |
16የሕዝቅያስ ልጅ የአጤር ዘሮች | 98 |
17የቤሳይ ዘሮች | 323 |
18የዮራ ዘሮች | 112 |
19የሐሱም ዘሮች | 223 |
20የጋቤር ዘሮች | 95 |
21የቤተ ልሔም ሰዎች#2፥21 ወይም ልጆች፣ ዘሮች | 123 |
22የነጦፋ ሰዎች | 56 |
23የዓናቶት ሰዎች | 128 |
24የዓዝሞት ዘሮች | 42 |
25የቂርያትይዓሪም#2፥25 የሰብዓ ሊቃናት ትርጕም (እንዲሁም ነህ 7፥29 ይመ)፤ ዕብራይስጡ ግን፣ ቂሪያት ኦሪም ይላል።፣ የከፊራና የብኤሮት ዘሮች | 743 |
26የራማና የጌባ ዘሮች | 621 |
27የማክማስ ሰዎች | 122 |
28የቤቴልና የጋይ ሰዎች | 223 |
29የናባው ዘሮች | 52 |
30የመጌብስ ዘሮች | 156 |
31የሌላው ኤላም ዘሮች | 1,254 |
32የካሪም ዘሮች | 320 |
33የሎድ፣ የሐዲድና | 725 |
34የኢያሪኮ ሰዎች | 345 |
35የሴናዓ ዘሮች | 3,630 |
36ካህናቱ፦
ከኢያሱ ቤተ ሰብ የዮዳኤ ዘሮች | 973 |
37የኢሜር ዘሮች | 1,052 |
38የፋስኮር ዘሮች | 1,247 |
39የካሪም ዘሮች | 1,017 |
40ሌዋውያኑ፦
በሆዳይዋ በኩል የኢያሱና የቀድምኤል ዘሮች | 74 |
41መዘምራኑ፦
የአሳፍ ዘሮች | 128 |
42የቤተ መቅደሱ በረኞች፦
የሰሎም፣ የአጤር፣ የጤልሞን፣ የዓቁብ፣ የሐጢጣና የሶባይ ዘሮች | 139 |
43የቤተ መቅደሱ አገልጋዮች፦
የሲሐ፣ የሐሡፋና የጠብዖት ዘሮች፤ |
44የኬራስ፣ የሲዓ፣ የፋዶን ዘሮች፤ |
45የልባና፣ የአጋባ፣ የዓቁብ ዘሮች፤ |
46የአጋብ፣ የሰምላይ፣ የሐናን ዘሮች፤ |
47የጌዴል፣ የጋሐር፣ የራያ ዘሮች፤ |
48የረአሶን፣ የኔቆዳ፣ የጋሴም ዘሮች፤ |
49የዖዛ፣ የፋሴሐ፣ የቤሳይ ዘሮች፤ |
50የአስና፣ የምዑናውያን፣ የንፉሰሲም ዘሮች፤ |
51የበቅቡቅ፣ የሐቁፋ፣ የሐርሑር ዘሮች፤ |
52የበስሎት፣ የምሒዳ፣ የሐርሳ ዘሮች፤ |
53የበርቆስ፣ የሲሣራ፣ የቴማ ዘሮች፤ |
54የንስያና የሐጢፋ ዘሮች። |
55የሰሎሞን አገልጋዮች ዘሮች፦
የሶጣይ፣ የሶፌሬት፣ የፍሩዳ ዘሮች፤ | |
56የየዕላ፣ የደርቆን፣ የጌዴል ዘሮች፤ | |
57የሰፋጥያስ፣ የሐጢል፣ | |
የፈክራት ሐፂቦይም፣ የአሚ ዘሮች፤ | |
58የቤተ መቅደሱ አገልጋዮችና የሰሎሞን አገልጋዮች ዘሮች | 392 |
---|
59ከዚህ የሚከተሉት ደግሞ ከቴልሜላ፣ ከቴላሬሳ፣ ከክሩብ፣ ከአዳንና ከኢሜር ከተሞች የመጡ ናቸው፤ ነገር ግን ቤተ ሰቦቻቸው የእስራኤል ዘር መሆናቸውን ማስረዳት አልቻሉም፦
60የዳላያ፣ የጦብያና የኔቆዳ ዘሮች | 652 |
61ከካህናቱ መካከል፦
የኤብያ፣ የአቆስና የቤርዜሊ ዘሮች፤ ቤርዜሊ በዚህ ስም ሊጠራ የቻለው የገለዓዳዊውን የቤርዜሊን ልጅ አግብቶ ስለ ነበር ነው።
62እነዚህ በትውልድ መዝገቡ ውስጥ የቤተ ሰባቸውን ዝርዝር ፈለጉ፤ ነገር ግን ማግኘት አልቻሉም፤ ስለዚህ እንዳልነጹ ተቈጥረው፣ ከክህነት አገልግሎት ተገለሉ። 63አገረ ገዥውም በኡሪምና በቱሚም እግዚአብሔርን የሚጠይቅ ካህን እስኪነሣ ድረስ፣ እጅግ ከተቀደሰው ምግብ እንዳይበሉ አዘዛቸው።
64ከምርኮ የተመለሱት ሰዎች ብዛት 42,360 ነበረ፤ 65ይህም 7,337 ከሚሆኑት ከወንዶችና ከሴቶች አገልጋዮቻቸው በተጨማሪ ነው፤ 200 ወንድና ሴት ዘማሪዎችም ነበሯቸው። 66736 ፈረሶች፣ 245 በቅሎዎች፣ 67435 ግመሎችና 6,720 አህዮች ነበሯቸው።
68በኢየሩሳሌም ወደሚገኘው ወደ እግዚአብሔር ቤት በደረሱ ጊዜ፣ አንዳንድ የቤተ ሰብ መሪዎች በቀድሞው ቦታ እንደ ገና ለሚሠራው የእግዚአብሔር ቤት በበጎ ፈቃድ ስጦታ አደረጉ። 69እንደየችሎታቸውም 61,000 የወርቅ ዳሪክ#2፥69 500 ኪሎ ግራም ያህል ነው።፣ 5,000 ምናን#2፥69 2.9 ሜትሪክ ቶን ያህል ነው። ብር፣ 100 ልብሰ ተክህኖ ለግምጃ ቤቱ ሰጡ።
70ካህናቱ፣ ሌዋውያኑ፣ መዘምራኑ፣ በር ጠባቂዎቹና የቤተ መቅደስ አገልጋዮቹ፣ ከሌሎች ሰዎች ጋር በየራሳቸው ከተሞች ሰፈሩ፤ የቀሩት እስራኤላውያንም በየከተሞቻቸው ተቀመጡ።
Currently Selected:
ዕዝራ 2: NASV
Highlight
Share
Copy
Want to have your highlights saved across all your devices? Sign up or sign in
መጽሐፍ ቅዱስ፣ አዲሱ መደበኛ ትርጕም™
የቅጅ መብት © 2001 በ Biblica, Inc.
ፈቃድ የተገኘባቸው ናቸው። መብቱ በመላው ዓለም በሕግ የተጠበቀ።
Holy Bible, New Amharic Standard Version™ (Addisu Medebegna Tirgum™)
Copyright © 2001 by Biblica, Inc.
Used with permission. All rights reserved worldwide.