ክርስቶስ የእኛ አሸናፊSample

ማቅረብ
በመዝሙረ ዳዊት 68:15–18መዝሙረኛው ህዝቡን በደህና ወደ እግዚአብሔር ተራራ በሚያደርሰው በእግዚአብሔር ኃይል ሲደሰት እናያለን፡፡ እንደ ክርስቲያን በወንጌል ውስጥ አንተና እኔ ወደ ዘላለማዊ ቤታችን በደህና የሚያደርሰን የፀና ተስፋ ተሰጥቶናል፡፡
በምዕራፉ ያለው ቁጥር 18 የሚያመለክተው ወደ ላይ ስላረገው ምርኮኞችንም በባቡሩ ከፊት እየመራ ስላለው ነው፡፡ ሐዋሪያው ጳውሎስ በኤፌሶን 4፡8 ላይ እየነገረን ያለው መዝሙረ ዳዊት 68:18 ስለ ክርስቶስ ኢየሱስና ከሞት በመነሳቱ የፈፀመውን የእርሱ መለኮታዊ ድል ይገልፃል እያለን ነው፡፡
ዕብራውያን 12:2የሚመክረን የእምነታችንን ራስና ፍፁም አድራጊ ኢየሱስ ላይ ዓይናችንን እንድናደርግ ነው፡፡ ራስና ፍፁም አድራጊ የሚለውን የግሪኩ ትርጉም በሚገርም ሁኔታ አሸናፊ ወይም ድል አድራጊ ይለዋል፡፡ በሌላ አገላለፅ ኢየሱስ ስለ እኛ ሀጢአትና ሞት በመስቀሉ ጦር ሜዳ ላይ ፍፁም ድል ተቀዳጅቷል፡፡ በሌላ አባባል ደግሞ ክርስቶስ መለኮታዊ አሸናፊያችን ነው!
በዚያ የወንጌል እውነት ምክንያት 1ኛ ቆሮንጦስ 6:14 የሚያስረግጥልን ያው ክርስቶስን ያስነሳው ኃይል ዛሬም በህይወታችን ያለውን ኃጢአት ሊያሸንፈው እንደሚችል አውቀን ማረፍ፤ እንዲሁም አንድ ቀን ደግሞ እንደሚያስነሳንና በእግዚአብሔር አብ ዘላለማዊ መገኘት ፊት እንደሚያቀርበን ነው፡፡
ክርስቲያኖች በዚህ ህይወት በምንም ሁኔታ ምንም ቢገጥመን የፀና የወንጌል ዋስትና አለን፤ ይኸውም አግዚአብሔር አንድ ቀን ወደ ዘላለማዊ ቤት ወደ እርሱ በደህና ያደርሰናል፡፡
About this Plan

በአሸናፊው በክርስቶስ በኩል እግዚአብሔር ለዘለዓለም ከሀጢአትና ከሞት ነፃ አውጥቶ ጠብቆናል፤ አሁንም በዚህ በወደቀ ዓለም ይጠብቀናል፤ አንድ ቀንም ወደ ራሱ በደህና ያደርሰናል፡፡
More
Related Plans

Immersed: Out of the Shallows Into the Deep

Running Our Race - Who Am I? And Why Am I Here?

A Kid's Guide To: Doing Hard Things With God

Same Page Summer

Is There Hope for My Marriage? One Good Reason to Stay Together

Trusting and Showing Trustworthiness: A 3-Day Marriage Plan

The Bible Recap - the Gospels

The Key to the Future You Want

Two-Year Chronological Bible Reading Plan (First Year-June)
