1
ወደ ሮም ሰዎች 4:20-21
አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም
አማ05
በእምነቱ ብርቱ ሆኖ ለእግዚአብሔር ክብር ሰጠ እንጂ እግዚአብሔር በሰጠው ተስፋ ባለማመን ከቶ አልተጠራጠረም። እግዚአብሔር የሰጠውንም ተስፋ የሚፈጽም መሆኑን በሙሉ ልብ ያምን ነበር።
Összehasonlít
Fedezd fel: ወደ ሮም ሰዎች 4:20-21
2
ወደ ሮም ሰዎች 4:17
ስለ አብርሃም፦ “የብዙ ሕዝብ አባት አድርጌሃለሁ” ተብሎ ተጽፎአል፤ ይህም ተስፋ ለአብርሃም የተሰጠው እርሱ የሞቱትን በሚያስነሣውና የሌለውን እንዲኖር በሚያደርገው አምላክ ስለ አመነ ነበር።
Fedezd fel: ወደ ሮም ሰዎች 4:17
3
ወደ ሮም ሰዎች 4:25
ይህ ጌታችን ኢየሱስም ስለ ኃጢአታችን ለሞት ተላልፎ የተሰጠውና እኛንም ለማጽደቅ ከሞት የተነሣው ነው።
Fedezd fel: ወደ ሮም ሰዎች 4:25
4
ወደ ሮም ሰዎች 4:18
አብርሃም ዘርህ እጅግ ይበዛል ተብሎ በተነገረው መሠረት የብዙ ሕዝብ አባት እንደሚሆን ያመነውና ተስፋ ያደረገው ምንም ተስፋ በማይጣልበት ነገር ነው።
Fedezd fel: ወደ ሮም ሰዎች 4:18
5
ወደ ሮም ሰዎች 4:16
ስለዚህ ተስፋው የተመሠረተው በእምነት ላይ ነበር፤ ይህም ተስፋ ለአብርሃም ዘሮች ሁሉ ከእግዚአብሔር በጸጋ የተሰጠ መሆኑ በዚህ ተረጋግጦአል። ይህም ሕግን ለሚከተሉት ሰዎች ብቻ ሳይሆን እንደ አብርሃም ላመኑ ሁሉ ነው፤ በዚህም መሠረት አብርሃም የሁላችንም አባት ነውና።
Fedezd fel: ወደ ሮም ሰዎች 4:16
6
ወደ ሮም ሰዎች 4:7-8
“በደላቸው ይቅር የተባለላቸውና ኃጢአታቸው የተደመሰሰላቸው ሰዎች የተባረኩ ናቸው! ጌታ ኃጢአቱን የማይቈጥርበት ሰው የተባረከ ነው!”
Fedezd fel: ወደ ሮም ሰዎች 4:7-8
7
ወደ ሮም ሰዎች 4:3
ቅዱስ መጽሐፍ “አብርሃም በእግዚአብሔር አመነ፤ እምነቱም ጽድቅ ሆኖ ተቈጠረለት” ይላል።
Fedezd fel: ወደ ሮም ሰዎች 4:3
Kezdőoldal
Biblia
Olvasótervek
Videók