YouVersion Logo
Search Icon

መዝሙረ ዳዊት 96

96
ከምርኮ በኋላ ቤት በተሠራ ጊዜ
1 # መዝ. 98፥1፤ ኢሳ. 42፥10። ለጌታ አዲስ መዝሙር ዘምሩ፥
ምድር ሁሉ፥ ለጌታ ዘምሩ።
2ለጌታ ዘምሩ ስሙንም ባርኩ፥
ዕለት ዕለትም ማዳኑን አውሩ።
3 # መዝ. 98፥4፤ 105፥1። ክብሩን ለአሕዛብ
ተኣምራቱንም ለሕዝቦች ሁሉ ንገሩ፥
4 # መዝ. 48፥2፤ 95፥3፤ 145፥3። ጌታ ታላቅ፥ ምስጋናውም ብዙ ነውና፥
ከአማልክትም ሁሉ በላይ የተፈራ ነውና።
5 # መዝ. 97፥7፤ 115፥4-8፤ ኢሳ. 40፥17፤ 1ቆሮ. 8፥4። የአሕዛብ አማልክት ሁሉ ጣዖቶች ናቸውና፥
ጌታ ግን ሰማያትን ሠራ።
6ክብርና ግርማ በፊቱ፥
ኃይልና ውበት በመቅደሱ ውስጥ ናቸው።
7የአሕዛብ ወገኖች፥ ለጌታ አቅርቡ፥
ክብርና ኃይልን ለጌታ አቅርቡ፥
8 # መዝ. 29፥2። ለስሙ የሚገባ ክብርን ለጌታ ስጡ፥
ቁርባን ያዙ፥ ወደ አደባባዮችም ግቡ።
9በቅድስናው ስፍራ ለጌታ ስገዱ፥
ምድር ሁሉ በፊቱ ትናወጥ።
10 # መዝ. 75፥4፤ 93፥1። በአሕዛብ መካከል፦ “ጌታ ነገሠ” በሉ።
እንዳይናወጥም ዓለሙን እርሱ አጸናው፥
አሕዛብንም በቅንነት ይፈርዳል።
11 # መዝ. 98፥7። ሰማያት ደስ ይበላቸው፥ ምድርም ሐሤትን ታድርግ፥
ባሕርና ሞላዋ ይናወጡ፥
12መስክና በእርሷም ያሉ ሁሉ ሐሤትን ያድርጉ፥
የዱር ዛፎችም ሁሉ በጌታ ፊት ደስ ይበላቸው፥
13 # መዝ. 98፥9። ይመጣልና፥ በምድር ላይ ሊፈርድ ይመጣልና፥
እርሱም ዓለምን በጽድቅ
አሕዛብንም በቅንነት ይፈርዳል።

Highlight

Share

Copy

None

Want to have your highlights saved across all your devices? Sign up or sign in

Video for መዝሙረ ዳዊት 96