መዝሙረ ዳዊት 61
61
1ለመዘምራን አለቃ፥ በበገናዎች፥ የዳዊት መዝሙር።
2አምላክ ሆይ፥ ጩኸቴን ስማ፥
ጸሎቴንም አድምጥ።
3ልቤ ተስፋ በቈረጠ ጊዜ ከምድር ዳርቻ ወደ አንተ እጮኻለሁ፥
ከፍ ባለ ዓለት ላይ ትመራኛለህ።
4 #
መዝ. 46፥2። በጠላት ፊት ጽኑ ግንብ፥
መጠጊያዬም ሆነኸኛልና።
5 #
መዝ. 17፥8፤ 36፥8፤ 57፥2። በድንኳንህ ለዘለዓለም እኖራለሁ፥
በክንፎችህም ጥላ እጋረዳለሁ፥
6አቤቱ፥ አንተ ስእለቴን ሰምተሃልና፥
ስምህንም ለሚፈሩ ርስትን ሰጠሃቸው።
7 #
መዝ. 21፥5። ለንጉሥ ከቀን በላይ ቀን ትጨምራለህ፥
ዓመታቱም ከትውልድ ወደ ትውልድ ይሆናሉ።
8 #
መዝ. 72፥5፤ 89፥5፤30፤37፤ 85፥11፤ 89፥15፤25፤ ምሳ. 20፥28። በእግዚአብሔር ፊት ለዘለዓለም ይኖራል፥
ይጠብቁት ዘንድ ቸርነትንና እውነትን አዘጋጅለት።
9እንዲሁ ለስምህ ለዘለዓለም እዘምራለሁ
ስእለቴን ሁልጊዜ እፈጽም ዘንድ።
Currently Selected:
መዝሙረ ዳዊት 61: መቅካእኤ
Highlight
Share
Copy

Want to have your highlights saved across all your devices? Sign up or sign in
መዝሙረ ዳዊት 61
61
1ለመዘምራን አለቃ፥ በበገናዎች፥ የዳዊት መዝሙር።
2አምላክ ሆይ፥ ጩኸቴን ስማ፥
ጸሎቴንም አድምጥ።
3ልቤ ተስፋ በቈረጠ ጊዜ ከምድር ዳርቻ ወደ አንተ እጮኻለሁ፥
ከፍ ባለ ዓለት ላይ ትመራኛለህ።
4 #
መዝ. 46፥2። በጠላት ፊት ጽኑ ግንብ፥
መጠጊያዬም ሆነኸኛልና።
5 #
መዝ. 17፥8፤ 36፥8፤ 57፥2። በድንኳንህ ለዘለዓለም እኖራለሁ፥
በክንፎችህም ጥላ እጋረዳለሁ፥
6አቤቱ፥ አንተ ስእለቴን ሰምተሃልና፥
ስምህንም ለሚፈሩ ርስትን ሰጠሃቸው።
7 #
መዝ. 21፥5። ለንጉሥ ከቀን በላይ ቀን ትጨምራለህ፥
ዓመታቱም ከትውልድ ወደ ትውልድ ይሆናሉ።
8 #
መዝ. 72፥5፤ 89፥5፤30፤37፤ 85፥11፤ 89፥15፤25፤ ምሳ. 20፥28። በእግዚአብሔር ፊት ለዘለዓለም ይኖራል፥
ይጠብቁት ዘንድ ቸርነትንና እውነትን አዘጋጅለት።
9እንዲሁ ለስምህ ለዘለዓለም እዘምራለሁ
ስእለቴን ሁልጊዜ እፈጽም ዘንድ።
Currently Selected:
:
Highlight
Share
Copy

Want to have your highlights saved across all your devices? Sign up or sign in