ትንቢተ ሚልክያስ መግቢያ
መግቢያ
ትንቢተ ሚልክያስ የተጻፈው ከክርስቶስ ልደት በፊት በአምስተኛው ምእተ ዓመት የኢየሩሳሌም ቤተ መቅደስ ዳግመኛ ከተሠራ በኋላ ነበር። ነቢዩ አጥብቆ የሚያሳስበው ካህናቱም ሆኑ ሕዝቡ ከእግዚአብሔር ጋር የገቡትን ቃል ኪዳን ማደስ እንዳለባቸው ነበር፤ መጽሐፉ የእግዚአብሔር ሕዝብ በአኗኗሩም ሆነ በአምልኮቱ መረን የተለቀቀና የተበላሸ እንደ ነበር ይገልጻል። ካህናቱና ሕዝቡ ተገቢውን መሥዋዕት ባለማቅረብና በሰጣቸውም መመሪያ ባለመኖር እግዚአብሔርን ለማታለል ይሞክሩ ነበር። እግዚአብሔር መንገዱን ለማዘጋጀትና ቃል ኪዳኑን ለማወጅ መልእክተኛውን አስቀድሞ እንደሚልክና በሕዝቡ ላይ ለመፍረድ እንደሚመጣ ትንቢቱ ይናገራል። “እነሆ ነቢዩን ኤልያስን እልክላችኋለሁ” የሚለው ትንቢት በአይሁድና በክርስቲያኖች ዘንድ ትልቅ ተቀባይነት አግኝቷል። ይሄው ትንቢት በወንጌል ውስጥም ተጠቅሶ ይገኛል።
አጠቃላይ የመጽሐፉ ይዘት
1. ጌታ ለእስራኤል ሕዝብ ያለው ፍቅር (1፥1-5)
2. የእግዚአብሔር ፍርድ በካህናት ላይ (1፥6—2፥9)
3. የቃል ኪዳን መፍረስ (2፥10-17)
4. የጌታ መምጣት (3፥1-4)
5. እግዚአብሔርን ማታለል የማይገባ መሆኑ (3፥5-15)
6. የታማኞች መሸለምና የክፉዎች መቀጣት (3፥16—4፥6)
ምዕራፍ
Currently Selected:
ትንቢተ ሚልክያስ መግቢያ: መቅካእኤ
Highlight
Share
Copy

Want to have your highlights saved across all your devices? Sign up or sign in
ትንቢተ ሚልክያስ መግቢያ
መግቢያ
ትንቢተ ሚልክያስ የተጻፈው ከክርስቶስ ልደት በፊት በአምስተኛው ምእተ ዓመት የኢየሩሳሌም ቤተ መቅደስ ዳግመኛ ከተሠራ በኋላ ነበር። ነቢዩ አጥብቆ የሚያሳስበው ካህናቱም ሆኑ ሕዝቡ ከእግዚአብሔር ጋር የገቡትን ቃል ኪዳን ማደስ እንዳለባቸው ነበር፤ መጽሐፉ የእግዚአብሔር ሕዝብ በአኗኗሩም ሆነ በአምልኮቱ መረን የተለቀቀና የተበላሸ እንደ ነበር ይገልጻል። ካህናቱና ሕዝቡ ተገቢውን መሥዋዕት ባለማቅረብና በሰጣቸውም መመሪያ ባለመኖር እግዚአብሔርን ለማታለል ይሞክሩ ነበር። እግዚአብሔር መንገዱን ለማዘጋጀትና ቃል ኪዳኑን ለማወጅ መልእክተኛውን አስቀድሞ እንደሚልክና በሕዝቡ ላይ ለመፍረድ እንደሚመጣ ትንቢቱ ይናገራል። “እነሆ ነቢዩን ኤልያስን እልክላችኋለሁ” የሚለው ትንቢት በአይሁድና በክርስቲያኖች ዘንድ ትልቅ ተቀባይነት አግኝቷል። ይሄው ትንቢት በወንጌል ውስጥም ተጠቅሶ ይገኛል።
አጠቃላይ የመጽሐፉ ይዘት
1. ጌታ ለእስራኤል ሕዝብ ያለው ፍቅር (1፥1-5)
2. የእግዚአብሔር ፍርድ በካህናት ላይ (1፥6—2፥9)
3. የቃል ኪዳን መፍረስ (2፥10-17)
4. የጌታ መምጣት (3፥1-4)
5. እግዚአብሔርን ማታለል የማይገባ መሆኑ (3፥5-15)
6. የታማኞች መሸለምና የክፉዎች መቀጣት (3፥16—4፥6)
ምዕራፍ
Currently Selected:
:
Highlight
Share
Copy

Want to have your highlights saved across all your devices? Sign up or sign in