YouVersion Logo
Search Icon

ኦሪት ዘሌዋውያን መግቢያ

መግቢያ
ኦሪት ዘሌዋውያን የሚያትተው በጥንታዊት እስራኤል ስለ ነበሩት የአምልኮ ደንቦችና ስለ ሃይማኖታዊ ሥርዓቶች ነው፤ እንዲሁም እነዚህን ሥርዓቶች በተግባር የመተርጐም ኀላፊነት ስለ ነበራቸው ካህናት ይገልጣል።
የመጽሐፉ ማእከላዊ ሐሳብ ስለ እግዚአብሔር ቅድስና የሚናገር ነው፤ እንዲሁም የእግዚአብሔር ሕዝብ ከዚሁ ቅዱስ ከሆነው ከእስራኤል አምላክ ጋር የቅርብ ግንኙነት ይኖራቸው ዘንድ፥ በእንዴት ያለ ሁኔታ ማምለክ እንደሚገባቸው ይዘረዝራል።
ከመጽሐፉ ውስጥ በጣም የታወቀው ትእዛዝ ኢየሱስ ሁለተኛው ታላቅ ትእዛዝ ብሎ የሠየመውና በም. 19 ቊ. 18 ላይ የሚገኘው ነው፤ እርሱም “ሰውን ሁሉ እንደ ራስህ አድርገህ ውደድ” የሚለው ነው።
አጠቃላይ የመጽሐፉ ይዘት
ሀ. የመባና የመሥዋዕት ሕግ 1፥1—7፥38
ለ. የአሮንና የልጆቹ የክህነት ሹመት 8፥1—10፥20
ሐ. ንጹሕ የሆነና ያልሆነ ነገር፥ እንዲሁም የመንጻት ሥርዓት 11፥1—15፥33
መ. የኃጢአት ስርየት ቀን 16፥1-34
ሠ. የቅድስና ሕይወትና የአምልኮ ሕግ 17፥1—27፥34

Highlight

Share

Copy

None

Want to have your highlights saved across all your devices? Sign up or sign in