1
ትንቢተ ኢሳይያስ 35:10
የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)
አማ2000
በእግዚአብሔር የተሰበሰቡም ይመለሳሉ፤ በደስታም ተመልሰው ወደ ጽዮን ይመጣሉ፤ የዘለዓለም ደስታም በራሳቸው ላይ ይሆናል፤ ሐሤትንና ደስታንም ያገኛሉ፤ መከራ፥ ኀዘንና ትካዜም ይጠፋሉ።
Compare
Explore ትንቢተ ኢሳይያስ 35:10
2
ትንቢተ ኢሳይያስ 35:3-4
ደካሞች እጆችና አንካሶች ጕልበቶች፥ ጽኑ። እናንተ አእምሮ የሌላችሁ፥ ልቡናችሁን አረጋጉ፤ ጽኑ፤ አትፍሩ፤ እነሆ፥ አምላካችን ፍርድን ይመልሳል፤ ይበቀላልም፤ እርሱም መጥቶ ያድነናል።
Explore ትንቢተ ኢሳይያስ 35:3-4
3
ትንቢተ ኢሳይያስ 35:8
በዚያም ንጹሕ መንገድ ይሆናል፤ እርሱም የተቀደሰ መንገድ ይባላል፤ በዚያም ንጹሓን ያልሆኑ አያልፉበትም፤ ርኩስ መንገድም በዚያ አይኖርም፤ የተበተኑትም በእርሱ ይሄዳሉ፤ አይሳሳቱምም።
Explore ትንቢተ ኢሳይያስ 35:8
4
ትንቢተ ኢሳይያስ 35:5
በዚያን ጊዜም የዕውሮች ዐይኖቻቸው ይገለጣሉ፤ የደንቆሮዎችም ጆሮዎች ይሰማሉ።
Explore ትንቢተ ኢሳይያስ 35:5
5
ትንቢተ ኢሳይያስ 35:6
በዚያን ጊዜ አንካሳዎች እንደ ሚዳቋ ይዘልላሉ፤ የዲዳዎችም ምላስ ርቱዕ ይሆናል፤ በምድረ በዳ ውኃ፥ በተጠማ መሬትም ፈሳሽ ይፈልቃልና።
Explore ትንቢተ ኢሳይያስ 35:6
Home
Bible
Plans
Videos