1
ኦሪት ዘፀአት 9:16
የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)
አማ2000
ነገር ግን ኀይሌን እገልጥብህ ዘንድ፥ ስሜም በምድር ሁሉ ላይ ይነገር ዘንድ ስለዚህ ጠበቅሁህ።
Compare
Explore ኦሪት ዘፀአት 9:16
2
ኦሪት ዘፀአት 9:1
እግዚአብሔርም ሙሴን አለው፥ “ወደ ፈርዖን ገብተህ እንዲህ በለው፦ የዕብራውያን አምላክ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ያመልኩኝ ዘንድ ሕዝቤን ልቀቅ።
Explore ኦሪት ዘፀአት 9:1
3
ኦሪት ዘፀአት 9:15
አሁን እጄን ዘርግቼ አንተን እመታሃለሁ፤ ሕዝብህንም እገድላቸዋለሁ፤ ምድራችሁም ትመታለች።
Explore ኦሪት ዘፀአት 9:15
4
ኦሪት ዘፀአት 9:3-4
እነሆ፥ የእግዚአብሔር እጅ በሜዳ ውስጥ በአሉት በከብቶችህ፥ በፈረሶችም፥ በአህዮችም፥ በግመሎችም፥ በበሬዎችም፥ በበጎችም ላይ ትሆናለች፤ ይኸውም እጅግ ጽኑዕ ሞት ነው፤ በዚያ ጊዜም በግብፃውያን ከብቶችና በእስራኤል ልጆች ከብቶች መካከል ልዩነት አደርጋለሁ። ከእስራኤልም ልጆች ከብቶች አንዳች አይሞትም።”
Explore ኦሪት ዘፀአት 9:3-4
5
ኦሪት ዘፀአት 9:18-19
እነሆ፥ ከተመሠረተች ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ እንደ እርሱ ያለ በግብፅ ሆኖ የማያውቅ እጅግ ታላቅ በረዶ ነገ በዚህ ጊዜ አዘንባለሁ። አሁን እንግዲህ ፥ ከብቶችህንም በሜዳም ያለህን ሁሉ ፈጥነህ ሰብስብ። በሜዳ የተገኘ ወደ ቤት ያልገባ ሰውና እንስሳ ሁሉ በረዶ ወርዶበት ይሞታልና።”
Explore ኦሪት ዘፀአት 9:18-19
6
ኦሪት ዘፀአት 9:9-10
እርሱም በግብፅ ሀገር ሁሉ ትቢያ ይሆናል፤ በግብፅም ሀገር ሁሉ በሰውና በእንስሳ ላይ ሻህኝ የሚያመጣ ቍስል ይሆናል” አላቸው። ሙሴም አመዱን በፈርዖን ፊት ወስዶ ወደ ሰማይ በተነው፤ በሰውና በእንስሳም ላይ ሻህኝ የሚያወጣ ቍስል ሆነ።
Explore ኦሪት ዘፀአት 9:9-10
Home
Bible
Plans
Videos