1
የያዕቆብ መልእክት 3:17
አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም
አማ05
ነገር ግን ከእግዚአብሔር የሚገኘው ጥበብ በመጀመሪያ ንጹሕ ነው፤ ቀጥሎም ሰላም ወዳድ፥ ደግ፥ ታዛዥ፥ ምሕረት አድራጊ፥ ጥሩ ፍሬ የሞላበት፥ አድልዎና ግብዝነት የሌለበት ነው።
Compare
Explore የያዕቆብ መልእክት 3:17
2
የያዕቆብ መልእክት 3:13
ከእናንተ መካከል ጥበበኛና አስተዋይ ሰው ማን ነው? በጥበብና በትሕትና የፈጸመውን ሥራ በመልካም አኗኗሩ ያሳይ።
Explore የያዕቆብ መልእክት 3:13
3
የያዕቆብ መልእክት 3:18
ሰላም ወዳድ ሰዎች ሰላምን ዘርተው የጽድቅን ፍሬ ይሰበስባሉ።
Explore የያዕቆብ መልእክት 3:18
4
የያዕቆብ መልእክት 3:16
ቅናትና ራስ ወዳድነት ባሉበት ስፍራ ሁከትና ክፉ ሥራ ሁሉ ይኖራሉ።
Explore የያዕቆብ መልእክት 3:16
5
የያዕቆብ መልእክት 3:9-10
በእርስዋ አባታችንን እግዚአብሔርን እናመሰግናለን፤ እንዲሁም በእርስዋ በእግዚአብሔር አምሳል የተፈጠሩትን ሰዎች እንረግማለን። ከአንድ አፍ ምስጋናና ርግማን ይወጣሉ፤ ወንድሞቼ ሆይ! ይህ ሊሆን አይገባም።
Explore የያዕቆብ መልእክት 3:9-10
6
የያዕቆብ መልእክት 3:6
ምላስም እንደ እሳት ናት፤ ምላስ በአካል ክፍሎቻችን መካከል የምትገኝ ክፉ ዓለም ናት፤ አካላችንን ትበክላለች፤ ከገሃነም እንደሚወጣ እሳትም የኑሮአችንን ሂደት ሁሉ ታቃጥላለች።
Explore የያዕቆብ መልእክት 3:6
7
የያዕቆብ መልእክት 3:8
ነገር ግን ምላስን ሊገራ የሚችል ማንም የለም፤ የሚገድል መርዝ የሞላባትና ዕረፍት የሌላት ክፉ ነገር ናት።
Explore የያዕቆብ መልእክት 3:8
8
የያዕቆብ መልእክት 3:1
ወንድሞቼ ሆይ! እኛ አስተማሪዎች የሆንን የባሰ ፍርድ እንደምንቀበል ታውቃላችሁና ከእናንተ ብዙዎች አስተማሪዎች አይሁኑ።
Explore የያዕቆብ መልእክት 3:1
Home
Bible
Plans
Videos