1
የዮሐንስ ወንጌል 8:12
የአማርኛ መጽሐፍ ቅዱስ (ሰማንያ አሃዱ)
አማ2000
ዳግመኛም ጌታችን ኢየሱስ፥ “የዓለም ብርሃን እኔ ነኝ፤ የሚከተለኝ የሕይወት ብርሃንን ያገኛል እንጂ በጨለማ ውስጥ አይመላለስም” ብሎ ተናገራቸው።
Linganisha
Chunguza የዮሐንስ ወንጌል 8:12
2
የዮሐንስ ወንጌል 8:32
እውነትንም ታውቋታላችሁ፤ እውነትም አርነት ታወጣችኋለች።”
Chunguza የዮሐንስ ወንጌል 8:32
3
የዮሐንስ ወንጌል 8:31
ጌታችን ኢየሱስም ያመኑበትን አይሁድ እንዲህ አላቸው፥ “እናንተም በቃሌ ጸንታችሁ ብትኖሩ በእውነት ደቀ መዛሙርቴ ናችሁ።
Chunguza የዮሐንስ ወንጌል 8:31
4
የዮሐንስ ወንጌል 8:36
ወልድ አርነት ካወጣችሁ በእውነት አርነት የወጣችሁ ናችሁ።
Chunguza የዮሐንስ ወንጌል 8:36
5
የዮሐንስ ወንጌል 8:7
ብዙ ጊዜ መላልሰው በጠየቁት ጊዜም ዐይኖቹን አንሥቶ፥ “ከእናንተ ኀጢኣት የሌለበት አስቀድሞ ድንጋይ ይጣልባት” አላቸው።
Chunguza የዮሐንስ ወንጌል 8:7
6
የዮሐንስ ወንጌል 8:34
ጌታችን ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አላቸው፥ “እውነት እውነት እላችኋለሁ፤ ኀጢኣትን የሚሠራ ሁሉ የኀጢኣት ባርያ ነው።
Chunguza የዮሐንስ ወንጌል 8:34
7
የዮሐንስ ወንጌል 8:10-11
ጌታችን ኢየሱስም ቀና ብሎ ወደ እርስዋ ተመለከተና እንዲህ አላት፥ “አንቺ ሴት፥ የሚከሱሽ ወዴት አሉ?” እርስዋም፥ “ጌታ ሆይ፥ የማየው የለም” ብላ መለሰችለት፤ ጌታችን ኢየሱስም፥ “እኔም አልፈርድብሽም፤ ወደ ቤትሽ ሂጂ፤ ከእንግዲህ ወዲህ ዳግመኛ ኀጢኣት አትሥሪ” አላት።
Chunguza የዮሐንስ ወንጌል 8:10-11
Nyumbani
Biblia
Mipango
Video