Лого на YouVersion
Икона за пребарување

ኦሪት ዘጸአት መግቢያ

መግቢያ
ኦሪት ዘጸአት የሚዘረዝረው የእስራኤል ሕዝብ በባርነት ይኖርበት ከነበረው ከግብጽ ምድር ስለ መውጣቱ ሁኔታ ነው፤ መጽሐፉ ሦስት ዋና ዋና ክፍሎች አሉት፦
1. ዕብራውያን ነጻ ስለ መውጣታቸውና ወደ ሲና ተራራ ስላደረጉት ጒዞ ይናገራል።
2. እግዚአብሔር ከሕዝቡ ጋር ቃል ኪዳን ስለ መግባቱና የሥነ ምግባር፥ የመተዳደሪያና የሃይማኖት ሕጎችን ለእነርሱ ስለ መስጠቱ ይናገራል።
3. ለእስራኤል፥ እንዲሁም ለካህናት ተግባርና ለእግዚአብሔር አምልኮ ስለ ተሰጡት ሕጎች ይናገራል።
ከሁሉም በላይ ይህ መጽሐፍ የሚያስረዳው እግዚአብሔር በባርነት ይኖሩ የነበሩትን ሕዝቡን ነጻ ካወጣ በኋላ፥ ለወደፊቱ ተስፋ ያላቸው ሕዝብ እንዲሆኑ እንዴት ይሠራ እንደ ነበር ነው።
በመጽሐፉ ውስጥ የጐላ ባለታሪክ ሆኖ የቀረበው ሰብአዊ ፍጡር፥ ሕዝቡን ከግብጽ እንዲያወጣለት እግዚአብሔር የመረጠው ሰው ሙሴ ነው፤ ከመጽሐፉ በጣም የታወቀው ክፍል ዐሥሩ ትእዛዞች የተዘረዘሩበት ምዕራፍ 20 ነው።
አጠቃላይ የመጽሐፉ ይዘት
የእስራኤል ከግብጽ ነጻ መውጣት 1፥1—15፥21
ሀ. ባርነት በግብጽ 1፥1-22
ለ. የሙሴ ልደትና ዕድገት 2፥1—4፥31
ሐ. ሙሴና አሮን በፈርዖን ፊት 5፥1—11፥10
መ. ፋሲካና ከግብጽ መውጣት 12፥1—15፥21
ከቀይ ባሕር እስከ ሲና ተራራ 15፥22—18፥27
ሕግና ቃል ኪዳን 19፥1—24፥18
የተቀደሰው ድንኳንና የአምልኮ ሥርዓት 25፥1—40፥38

Нагласи

Сподели

Копирај

None

Дали сакаш да ги зачуваш Нагласувањата на сите твои уреди? Пријави се или најави се