1
1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 13:4-5
መጽሐፍ ቅዱስ - (ካቶሊካዊ እትም - ኤማሁስ)
መቅካእኤ
ፍቅር ይታገሳል፤ ቸርነትንም ያደርጋል። ፍቅር አይቀናም፤ አይመካም፤ አይታበይም፤ ተገቢ ያልሆነ ነገር አያደርግም፤ ራስ ወዳድ አይደለም፤ አይበሳጭም፥ በደልን አይቆጥርም።
比較
1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 13:4-5で検索
2
1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 13:7
ፍቅር ሁሉን ይታገሣል፤ ሁሉን ያምናል፤ ሁሉን ተስፋ ያደርጋል፤ በሁሉ ነገር ይጸናል።
1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 13:7で検索
3
1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 13:6
ከእውነት ጋር ደስ ይለዋል እንጂ በዐመፅ ደስ አይሰኝም።
1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 13:6で検索
4
1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 13:13
እንግዲህ እምነት፥ ተስፋ፥ ፍቅር እነዚህ ሦስቱ ጸንተው ይኖራሉ፤ ከእነዚህም የሚበልጠው ፍቅር ነው።
1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 13:13で検索
5
1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 13:8
ፍቅር ከቶ አይወድቅም፤ ትንቢት የመናገር ስጦታም ቢሆን ይሻራል፤ ልሳንም ቢሆን ይቀራል፤ ዕውቀትም ቢሆን ያልፋል።
1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 13:8で検索
6
1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 13:1
በሰዎችና በመላእክት ልሳን ብናገር፥ ፍቅር ግን ከሌለኝ እንደሚጮኽ ናስ ወይም እንደሚንሿሿ ጸናጽል ነኝ።
1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 13:1で検索
7
1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 13:2
ትንቢት የመናገር ስጦታ ቢኖረኝ፥ ምስጢርን ሁሉ ባውቅ፥ ዕውቀትን ሁሉ ብረዳ፥ ተራሮችንም እስካፈልስ ድረስ እምነት ሁሉ ቢኖረኝ ፍቅር ግን ከሌለኝ ከንቱ ነኝ።
1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 13:2で検索
8
1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 13:3
ያለኝን ሁሉ ለድኾች ባካፍል፥ ሰውነቴንም እንዲቃጠል ለእሳት አሳልፌ ብሰጥ፥ ፍቅር ግን ከሌለኝ ምንም አይጠቅመኝም።
1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 13:3で検索
9
1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 13:11
ልጅ ሳለሁ እንደ ልጅ እናገር ነበር፤ እንደ ልጅ አስብ ነበር፤ እንደ ልጅም አሰላስል ነበር። ሙሉ ሰው በሆንኩ ጊዜ ግን የልጅነትን ጠባይ ትቻለሁ።
1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 13:11で検索
ホーム
聖書
読書プラン
ビデオ