መጽሐፈ ሲራክ 41
41
ስለ ሞት
1ሞት ሆይ፥ ሰው በደኅና ሲኖር፥
በሁሉ ተዘጋጅቶ ሳለ፥ ኀይልም ሳለው፥
ለመብላትም ሆዱ ተከፍቶ ሳለ፥
በሰው ላይ በምትመጣ ጊዜ ስም አጠራርህ እንዴት መራራ ነው!
2ሞት ሆይ፥ ኀይል በሌለው፥ ፈጽሞም ባረጀ፥
ሊያደርገውም የሚችል ምንም በሌለው፥ የሚያውቀውም በሌለው፥
በድሃ ሰው ላይ በምትመጣ ጊዜ ፍርድህ እንዴት መልካም ነው!
3የሞትን ፍርድ አትፍራ፤
ከአንተም በፊት የነበሩትንና ከአንተም በኋላ የሚነሡትን አስባቸው።
የእግዚአብሔር ፍርድ በሰው ሁሉ ላይ ነው፤
4እንግዲህ የእግዚአብሔርን ፈቃድ ለምን ትነቅፋለህ?
ዐሥር ዓመት፥ መቶ ዓመት፥ ሺህ ዓመትም በሕይወት ብትኖር፥
ከሞት ጋራ ክርክር የለህም።
5የኀጢአተኞች ሰዎች ልጆች ጐስቋሎች ልጆች ይሆናሉ፤
የክፉዎች ሰዎችም ቤታቸው ይፈርሳል።
6የኀጢአተኞች ልጆች ርስታቸውን ያጣሉ፤
ኀጢአታቸውም ከዘራቸው ጋር አደገ።
7ስለ እርሱ ይዋረዳሉና፥
የኀጢአተኛ አባት ልጆች ይጐሰቍላሉ።
8የልዑል እግዚአብሔርን ሕግ ላፈረሳችሁ
ኀጢአተኞች ሰዎች ወዮላችሁ!
9ብትወልዱም ለርግማን ትወልዳላቸሁ፤
ብትሞቱም ዕድል ፋንታችሁ ርግማን ነው።
10ሁሉ ከምድር ተፈጠረ፤ መመለሻውም ወደ ምድር ነው፤
ኀጢአተኞችም እንዲሁ ከርግማን ወደ ጥፋት ይሄዳሉ።
11የሰው ኀዘኑ ስለ ሰውነቱ ነው፤
የኀጢአተኞችም ስማቸው ይደመሰሳል።
12መልካም ስምን ታስጠራ ዘንድ አስብ፤
ከሺህ ታላላቅ የወርቅ መዛግብትም እርሱ ብቻ ይቀርሃል።
13በዘመንህ ቍጥር በደስታ መኖር መልካም ነው፤
እርሱ ለዘለዓለም ጸንቶ ይኖርልሃልና መልካም ስም ይሻላል።
14ጥበብ ግን ልጆችዋን በሰላም ትጠብቃቸዋለች፤
የተሰወረ ጥበብና የማይታይ ድልብ፥ የሁለቱ ጥቅማቸው ምንድን ነው?
15ጥበቡን ከሚሰውር ሰው፤
ስንፍናውን የሚሰውር ሰው ይሻላል።
16እንግዲህ ቃሌንና ጥበቤን#“ጥበቤን” የሚለው በግሪክ ሰባ. ሊ. የለም። እፈሩ፤
የሚያፍር ሁሉ በበጎ ይጠበቃል፤
በሁሉ ይማከር ዘንድ ሁሉ የታመነ አይደለም።#ግሪክ ሰባ. ሊ. “... ኀፍረትን መጠበቅ መልካም አይደለምና በማንኛውም ነገር ሁሉን ማረጋገጥ አይቻልምና” ይላል።
17ልጅ እንወልዳለን ብለው በዝሙት መኖር፤
ለአባትና ለእናት ኀፍረት ነው#ግሪክ ሰባ. ሊ. “በአባትና በእናት ፊት አመንዝራ ከመሆን እፈሩ” ይላል። ለአለቃና ለታላላቆችም መዋሸት ኀፍረት ነው።
18ለሹምና ለዳኛ ቃል መለወጥ ኀፍረት ነው።
ለማኅበርና ለሕዝብም መሳት ኀፍረት ነው፤
ከጓደኛህና ከወዳጅህ ጋር መከዳዳት ኀፍረት ነው።
19ለእንግዳ በእንግድነት ካደረበት ቤት ሰርቆ መሄድ ኀፍረት ነው፤
የእግዚአብሔርንም እውነትና ቃል ኪዳን ማፍረስ ኀፍረት ነው፤
የሌላ ሰው እህል ለመብላት በመስገብገብ መቅረብ ኀፍረት ነው፤
አደራ ከአስጠበቁህ ገንዝብና ከባልንጀራህ ገንዘብ መስረቅ ኀፍረት ነው።#ግሪክ ሰባ. ሊ. ልዩ ነው።
20የሚጠራህን ሰው ቸል ማለት ኀፍረት ነው፤#ግሪኩ “ሰላምታ ለሚሰጥህ ሰላምታን አለመስጠት” ይላል።
ወደ ሌላ ሰው ሚስትም መመልከት ኀፍረት ነው።
21በመከራው ጊዜ ባልንጀራህን ቸል ማለት ኀፍረት ነው፤
በሌላ ሰው ገንዘብም መሳሳት ኀፍረት ነው።
የጎልማሳ ሚስት ማነጋገርም ኀፍረት ነው።
22ገረዱንም አታባብላት፤ ወደ መኝታዋም አትቅረብ፤
ወዳጅህን መሳደብ ኀፍረት ነው፤
ከሰጠኸውም በኋላ አትሳደብ፤ የሰማኸውን ነገር ማውጣት፥ መናገርም ኀፍረት ነው።
ምሥጢርንም መግለጥ ኀፍረት ነው፤
23ይህን ብትጠብቅ በእውነት ኀፊረ ገጽ ያለህ ትሆናለህ፤
በሰውም ሁሉ ዘንድ መወደድን ታገኛለህ።
Currently Selected:
መጽሐፈ ሲራክ 41: አማ2000
ማድመቅ
ያጋሩ
ኮፒ

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ
መጽሐፈ ሲራክ 41
41
ስለ ሞት
1ሞት ሆይ፥ ሰው በደኅና ሲኖር፥
በሁሉ ተዘጋጅቶ ሳለ፥ ኀይልም ሳለው፥
ለመብላትም ሆዱ ተከፍቶ ሳለ፥
በሰው ላይ በምትመጣ ጊዜ ስም አጠራርህ እንዴት መራራ ነው!
2ሞት ሆይ፥ ኀይል በሌለው፥ ፈጽሞም ባረጀ፥
ሊያደርገውም የሚችል ምንም በሌለው፥ የሚያውቀውም በሌለው፥
በድሃ ሰው ላይ በምትመጣ ጊዜ ፍርድህ እንዴት መልካም ነው!
3የሞትን ፍርድ አትፍራ፤
ከአንተም በፊት የነበሩትንና ከአንተም በኋላ የሚነሡትን አስባቸው።
የእግዚአብሔር ፍርድ በሰው ሁሉ ላይ ነው፤
4እንግዲህ የእግዚአብሔርን ፈቃድ ለምን ትነቅፋለህ?
ዐሥር ዓመት፥ መቶ ዓመት፥ ሺህ ዓመትም በሕይወት ብትኖር፥
ከሞት ጋራ ክርክር የለህም።
5የኀጢአተኞች ሰዎች ልጆች ጐስቋሎች ልጆች ይሆናሉ፤
የክፉዎች ሰዎችም ቤታቸው ይፈርሳል።
6የኀጢአተኞች ልጆች ርስታቸውን ያጣሉ፤
ኀጢአታቸውም ከዘራቸው ጋር አደገ።
7ስለ እርሱ ይዋረዳሉና፥
የኀጢአተኛ አባት ልጆች ይጐሰቍላሉ።
8የልዑል እግዚአብሔርን ሕግ ላፈረሳችሁ
ኀጢአተኞች ሰዎች ወዮላችሁ!
9ብትወልዱም ለርግማን ትወልዳላቸሁ፤
ብትሞቱም ዕድል ፋንታችሁ ርግማን ነው።
10ሁሉ ከምድር ተፈጠረ፤ መመለሻውም ወደ ምድር ነው፤
ኀጢአተኞችም እንዲሁ ከርግማን ወደ ጥፋት ይሄዳሉ።
11የሰው ኀዘኑ ስለ ሰውነቱ ነው፤
የኀጢአተኞችም ስማቸው ይደመሰሳል።
12መልካም ስምን ታስጠራ ዘንድ አስብ፤
ከሺህ ታላላቅ የወርቅ መዛግብትም እርሱ ብቻ ይቀርሃል።
13በዘመንህ ቍጥር በደስታ መኖር መልካም ነው፤
እርሱ ለዘለዓለም ጸንቶ ይኖርልሃልና መልካም ስም ይሻላል።
14ጥበብ ግን ልጆችዋን በሰላም ትጠብቃቸዋለች፤
የተሰወረ ጥበብና የማይታይ ድልብ፥ የሁለቱ ጥቅማቸው ምንድን ነው?
15ጥበቡን ከሚሰውር ሰው፤
ስንፍናውን የሚሰውር ሰው ይሻላል።
16እንግዲህ ቃሌንና ጥበቤን#“ጥበቤን” የሚለው በግሪክ ሰባ. ሊ. የለም። እፈሩ፤
የሚያፍር ሁሉ በበጎ ይጠበቃል፤
በሁሉ ይማከር ዘንድ ሁሉ የታመነ አይደለም።#ግሪክ ሰባ. ሊ. “... ኀፍረትን መጠበቅ መልካም አይደለምና በማንኛውም ነገር ሁሉን ማረጋገጥ አይቻልምና” ይላል።
17ልጅ እንወልዳለን ብለው በዝሙት መኖር፤
ለአባትና ለእናት ኀፍረት ነው#ግሪክ ሰባ. ሊ. “በአባትና በእናት ፊት አመንዝራ ከመሆን እፈሩ” ይላል። ለአለቃና ለታላላቆችም መዋሸት ኀፍረት ነው።
18ለሹምና ለዳኛ ቃል መለወጥ ኀፍረት ነው።
ለማኅበርና ለሕዝብም መሳት ኀፍረት ነው፤
ከጓደኛህና ከወዳጅህ ጋር መከዳዳት ኀፍረት ነው።
19ለእንግዳ በእንግድነት ካደረበት ቤት ሰርቆ መሄድ ኀፍረት ነው፤
የእግዚአብሔርንም እውነትና ቃል ኪዳን ማፍረስ ኀፍረት ነው፤
የሌላ ሰው እህል ለመብላት በመስገብገብ መቅረብ ኀፍረት ነው፤
አደራ ከአስጠበቁህ ገንዝብና ከባልንጀራህ ገንዘብ መስረቅ ኀፍረት ነው።#ግሪክ ሰባ. ሊ. ልዩ ነው።
20የሚጠራህን ሰው ቸል ማለት ኀፍረት ነው፤#ግሪኩ “ሰላምታ ለሚሰጥህ ሰላምታን አለመስጠት” ይላል።
ወደ ሌላ ሰው ሚስትም መመልከት ኀፍረት ነው።
21በመከራው ጊዜ ባልንጀራህን ቸል ማለት ኀፍረት ነው፤
በሌላ ሰው ገንዘብም መሳሳት ኀፍረት ነው።
የጎልማሳ ሚስት ማነጋገርም ኀፍረት ነው።
22ገረዱንም አታባብላት፤ ወደ መኝታዋም አትቅረብ፤
ወዳጅህን መሳደብ ኀፍረት ነው፤
ከሰጠኸውም በኋላ አትሳደብ፤ የሰማኸውን ነገር ማውጣት፥ መናገርም ኀፍረት ነው።
ምሥጢርንም መግለጥ ኀፍረት ነው፤
23ይህን ብትጠብቅ በእውነት ኀፊረ ገጽ ያለህ ትሆናለህ፤
በሰውም ሁሉ ዘንድ መወደድን ታገኛለህ።