መጽሐፈ ሲራክ 39
39
1ጥበብስ በቀደሙ ሰዎች ሁሉ ዘንድ ተመረመረች።
2በሃይማኖት ስማቸውን ላስጠሩ ሰዎች ትንቢትን ታስተምራለች፤
ወደ ነቢያትም ምሳሌ ታገባለች።
3የተሰወረውንም ምሳሌ ትመረምራለች፤
ምሳሌውንም ወደ መተርጐም ትመልሳለች።#ምዕ. 39 ከቍ. 1 እስከ 3 በግሪክ ሰባ. ሊ. ልዩ ነው።
4በመኳንንትም መካከል ትጠቅማለች፤
በአለቆችም መካከል ትታያለች፤
ልዩ ወደ ሆኑ ወደ አሕዛብም ሀገር ትገባለች፤
5ሰዎችን በበጎም፥ በክፉም ትፈትናቸዋለችና፥
ወደ ፈጣሪው ወደ እግዚአብሔር ይሄድ ዘንድ፥
በልዑልም ፊት ይጸልይ ዘንድ ልቡን ይመልሳል፤
አፉንም ይከፍታል፤ ይለምናልም፤ ስለ ኀጢአቱም ይናዘዛል።
6ነገር ግን ገናና የሆነው እግዚአብሔር ከፈቀደ፥
የጥበብንም መንፈስ ካሳደረበት፥ እርሱ የጥበቡን ነገር ያፈልቃል፤
በጸሎቱም ለእግዚአብሔር ይገዛል።
7እርሱም ጥበብንና ምክርን ይገልጥለታል፤
የተሰወረውንም ያውቅ ዘንድ ያሳስበዋል።
8እርሱም የትምህርቱን ጥበብ ያሳያል፤
በእግዚአብሔር የኪዳን ሕግም ይመካል።
9ስለ ጥበቡም ብዙ ሰዎች ያመሰግኑታል፤
ለዘለዓለሙም አይደመሰስም፤ ስም አጠራሩም አይጠፋም፤
ስሙም ለልጅ ልጅ ጸንቶ ይኖራል።
10አሕዛብም ጥበቡን ይናገራሉ፤
በሸንጎ መካከልም ያመሰግኑታል።
11ከሺህ ልጅ ስምን ማስጠራት ይሻላል፤
ከሞተም በኋላ ሥራው ጸንቶ ይኖራል።
የምስጋና መዝሙር
12ዳግመኛም አስቤ እናገራለሁ፤
እንደ ሙሉ ጨረቃ ሙሉ ነኝና።
13የጻድቃን ልጆች ስሙኝ፤ ለምልሙ፤ ታደሱ፤
አበባ በምድረ በዳ ጠል እንደሚያብብ አብቡ።
14እንደ ሊባኖስ መዓዛ መዓዛችሁ ይጣፍጥ፤
አበባችሁን እንደ ጽጌረዳ አብቅሉ ፤
መዓዛችሁንም አጣፍጡ፤
መዝሙርን ዘምሩ፤ በሥራውም ሁሉ እግዚአብሔርን አመስግኑት።
15ስሙን አግንኑት፤
በአንድ ሺህ#ግሪኩ “በከንፈራችሁ መዝሙር” ይላል። መዝሙርና በመሰንቆ ስሙን አግንኑት
በምታመሰግኑትም ጊዜ እንዲህ በሉ።
16“የእግዚአብሔር ሥራው ገናና ነው።
እጅግም ያማረ ነው፤ ሥርዐቱም ሁሉ በየጊዜው ነው።”
17“ይህ ለምንድን ነው? ያስ ለምንድን ነው?” ማለት አይገባም፤
ሁሉም በጊዜው ይፈቀዳል፤
ውኃውንም በቃሉ እንደ ግድግዳ አጸናው፤
በአፉ ቃልም እንደ ኵሬ ውኃ፤
18በትእዛዙም ሁሉ የተወደደ ነው፤
መድኀኒትነቱንም የሚያጐድል የለም።
19የሰው ሁሉ ሥራ በፊቱ ነው፤
ከዐይኖቹም ፊት መሰወር የሚችል የለም።
20ዓለም ሳይፈጠር እስከ ዘለዓለም ድረስ ሁሉን ዐወቀ፤
በፊቱም ምንም ልዩ ፍጥረት የለም።
21ሁሉም ለመፍቅዳቸው ተፈጥሯልና
“ይህ ለምንድን ነው? ያስ ለምንድን ነው?” የሚል የለም።
22በረከቱም እንደ ፈሳሽ ውኃ መላች፤
እንደ ጎርፍ ውኃም ምድርን አረካቻት፤
23እንደዚሁ ቍጣው አሕዛብን ከፈለቻቸው።
24የጻድቅ መንገዱ የቀና ነው፤
የኃጥእ መንገድ ግን ዕንቅፋት ነው፤
ውኃውንም የሚለውጠው፥ ጨውም የሚያደርገው እርሱ ነው።
25በጎ ነገር ከጥንት ጀምሮ ለበጎ ሰዎች ተፈጠረች፤
እንደዚሁ ክፉ ነገርም ለኃጢአተኞች ተፈጠረች።
26የሰው የመፍቅዱ ሁሉ መጀመሪያ፥
ውኃ፥ እሳት፥ ብረት፥ ጨው፥ እህል፥ ስንዴ፥
ማር፥ ወተት፥ ወይን፥ ዘይትና ልብስ ነው።
27ይህ ሁሉ ለጻድቃን ሰዎች በረከታቸው ነው፤
እንደዚሁም ሁሉ በኀጢአተኞች ሰዎች ወደ ክፉ ይመለስባቸዋል።
28ለበቀል የተፈጠረች መንፈስ አለች፤
በጥፋታቸው መቅሠፍታቸውን ያበዟታል፤
በዘመናቸው ኀይላቸው ይደክማል፤
የፈጣሪያቸው መቅሠፍትም ይመጣባቸዋል።
29እሳት፥ በረድ፥ ረኃብና ቸነፈር ይህ ሁሉ ለበቀል ተፈጠረ።
30የምድር አራዊት ጥርስ ጊንጥና እፉኝት፥
ጦርም ኀጢአተኞችን ታጠፋቸው ዘንድ ተፈጠረች።
31እርሱ ግን በይቅርታው ደስ ያሰኛል፤
የዓለምንም መፍቅድ ያዘጋጃል።
ሁሉም ጊዜው ከደረሰ ከዕድሜው አያልፍም።
32ስለዚህ ነገር ከጥንት ጀምሮ ሁሉም ተዘጋጀ፤
ይህንም አስቤ በመጽሐፍ ጻፍሁት።
33የእግዚአብሔር ሥራው ሁሉ ያማረ ነውና፤
ለሰውም በየጊዜው መፍቅዱን ይሰጣል።
34“ይህን ክፉ ፈጠርህ፤ ያንም አሳመርህ” የሚለው የለም።
ሁሉን ቀኑ ይገልጠዋልና።
35አሁንም በፍጹም ልቡናችሁ፤ በፍጹምም አንደበታችሁ እግዚአብሔርን አመስግኑት፤
ሁልጊዜም ለስሙ ምስጋና አቅርቡ።
Currently Selected:
መጽሐፈ ሲራክ 39: አማ2000
ማድመቅ
ያጋሩ
ኮፒ

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ
መጽሐፈ ሲራክ 39
39
1ጥበብስ በቀደሙ ሰዎች ሁሉ ዘንድ ተመረመረች።
2በሃይማኖት ስማቸውን ላስጠሩ ሰዎች ትንቢትን ታስተምራለች፤
ወደ ነቢያትም ምሳሌ ታገባለች።
3የተሰወረውንም ምሳሌ ትመረምራለች፤
ምሳሌውንም ወደ መተርጐም ትመልሳለች።#ምዕ. 39 ከቍ. 1 እስከ 3 በግሪክ ሰባ. ሊ. ልዩ ነው።
4በመኳንንትም መካከል ትጠቅማለች፤
በአለቆችም መካከል ትታያለች፤
ልዩ ወደ ሆኑ ወደ አሕዛብም ሀገር ትገባለች፤
5ሰዎችን በበጎም፥ በክፉም ትፈትናቸዋለችና፥
ወደ ፈጣሪው ወደ እግዚአብሔር ይሄድ ዘንድ፥
በልዑልም ፊት ይጸልይ ዘንድ ልቡን ይመልሳል፤
አፉንም ይከፍታል፤ ይለምናልም፤ ስለ ኀጢአቱም ይናዘዛል።
6ነገር ግን ገናና የሆነው እግዚአብሔር ከፈቀደ፥
የጥበብንም መንፈስ ካሳደረበት፥ እርሱ የጥበቡን ነገር ያፈልቃል፤
በጸሎቱም ለእግዚአብሔር ይገዛል።
7እርሱም ጥበብንና ምክርን ይገልጥለታል፤
የተሰወረውንም ያውቅ ዘንድ ያሳስበዋል።
8እርሱም የትምህርቱን ጥበብ ያሳያል፤
በእግዚአብሔር የኪዳን ሕግም ይመካል።
9ስለ ጥበቡም ብዙ ሰዎች ያመሰግኑታል፤
ለዘለዓለሙም አይደመሰስም፤ ስም አጠራሩም አይጠፋም፤
ስሙም ለልጅ ልጅ ጸንቶ ይኖራል።
10አሕዛብም ጥበቡን ይናገራሉ፤
በሸንጎ መካከልም ያመሰግኑታል።
11ከሺህ ልጅ ስምን ማስጠራት ይሻላል፤
ከሞተም በኋላ ሥራው ጸንቶ ይኖራል።
የምስጋና መዝሙር
12ዳግመኛም አስቤ እናገራለሁ፤
እንደ ሙሉ ጨረቃ ሙሉ ነኝና።
13የጻድቃን ልጆች ስሙኝ፤ ለምልሙ፤ ታደሱ፤
አበባ በምድረ በዳ ጠል እንደሚያብብ አብቡ።
14እንደ ሊባኖስ መዓዛ መዓዛችሁ ይጣፍጥ፤
አበባችሁን እንደ ጽጌረዳ አብቅሉ ፤
መዓዛችሁንም አጣፍጡ፤
መዝሙርን ዘምሩ፤ በሥራውም ሁሉ እግዚአብሔርን አመስግኑት።
15ስሙን አግንኑት፤
በአንድ ሺህ#ግሪኩ “በከንፈራችሁ መዝሙር” ይላል። መዝሙርና በመሰንቆ ስሙን አግንኑት
በምታመሰግኑትም ጊዜ እንዲህ በሉ።
16“የእግዚአብሔር ሥራው ገናና ነው።
እጅግም ያማረ ነው፤ ሥርዐቱም ሁሉ በየጊዜው ነው።”
17“ይህ ለምንድን ነው? ያስ ለምንድን ነው?” ማለት አይገባም፤
ሁሉም በጊዜው ይፈቀዳል፤
ውኃውንም በቃሉ እንደ ግድግዳ አጸናው፤
በአፉ ቃልም እንደ ኵሬ ውኃ፤
18በትእዛዙም ሁሉ የተወደደ ነው፤
መድኀኒትነቱንም የሚያጐድል የለም።
19የሰው ሁሉ ሥራ በፊቱ ነው፤
ከዐይኖቹም ፊት መሰወር የሚችል የለም።
20ዓለም ሳይፈጠር እስከ ዘለዓለም ድረስ ሁሉን ዐወቀ፤
በፊቱም ምንም ልዩ ፍጥረት የለም።
21ሁሉም ለመፍቅዳቸው ተፈጥሯልና
“ይህ ለምንድን ነው? ያስ ለምንድን ነው?” የሚል የለም።
22በረከቱም እንደ ፈሳሽ ውኃ መላች፤
እንደ ጎርፍ ውኃም ምድርን አረካቻት፤
23እንደዚሁ ቍጣው አሕዛብን ከፈለቻቸው።
24የጻድቅ መንገዱ የቀና ነው፤
የኃጥእ መንገድ ግን ዕንቅፋት ነው፤
ውኃውንም የሚለውጠው፥ ጨውም የሚያደርገው እርሱ ነው።
25በጎ ነገር ከጥንት ጀምሮ ለበጎ ሰዎች ተፈጠረች፤
እንደዚሁ ክፉ ነገርም ለኃጢአተኞች ተፈጠረች።
26የሰው የመፍቅዱ ሁሉ መጀመሪያ፥
ውኃ፥ እሳት፥ ብረት፥ ጨው፥ እህል፥ ስንዴ፥
ማር፥ ወተት፥ ወይን፥ ዘይትና ልብስ ነው።
27ይህ ሁሉ ለጻድቃን ሰዎች በረከታቸው ነው፤
እንደዚሁም ሁሉ በኀጢአተኞች ሰዎች ወደ ክፉ ይመለስባቸዋል።
28ለበቀል የተፈጠረች መንፈስ አለች፤
በጥፋታቸው መቅሠፍታቸውን ያበዟታል፤
በዘመናቸው ኀይላቸው ይደክማል፤
የፈጣሪያቸው መቅሠፍትም ይመጣባቸዋል።
29እሳት፥ በረድ፥ ረኃብና ቸነፈር ይህ ሁሉ ለበቀል ተፈጠረ።
30የምድር አራዊት ጥርስ ጊንጥና እፉኝት፥
ጦርም ኀጢአተኞችን ታጠፋቸው ዘንድ ተፈጠረች።
31እርሱ ግን በይቅርታው ደስ ያሰኛል፤
የዓለምንም መፍቅድ ያዘጋጃል።
ሁሉም ጊዜው ከደረሰ ከዕድሜው አያልፍም።
32ስለዚህ ነገር ከጥንት ጀምሮ ሁሉም ተዘጋጀ፤
ይህንም አስቤ በመጽሐፍ ጻፍሁት።
33የእግዚአብሔር ሥራው ሁሉ ያማረ ነውና፤
ለሰውም በየጊዜው መፍቅዱን ይሰጣል።
34“ይህን ክፉ ፈጠርህ፤ ያንም አሳመርህ” የሚለው የለም።
ሁሉን ቀኑ ይገልጠዋልና።
35አሁንም በፍጹም ልቡናችሁ፤ በፍጹምም አንደበታችሁ እግዚአብሔርን አመስግኑት፤
ሁልጊዜም ለስሙ ምስጋና አቅርቡ።