መጽሐፈ ሲራክ 37
37
1ወዳጅ ያበጀ ሰው ሁሉ እኔም ወዳጁ ነኝ ይላል፤
ነገር ግን በከንቱ ለስም ወዳጅ የሚሆን ሰው አለ።
2በልቡናው ግን እስከሚሞትበት ቀን ድረስ ኀዘን ይኖራል፤
ጠላት የሚሆን ወዳጅም አለ።
3ክፉ ምኞት ሆይ! ከወዴት ተገኘሽ፤
በምድሩ ሁሉ ኀጢአትን መላሽ።
4በደስታህ ጊዜ የሚቀርብህ ወዳጅ አለ፤
ብትቸገር ግን እርሱ ጠላት ይሆንሃል።
5በበሽታህ ጊዜ ስለ ሆዱ የሚያዝንልህ ወዳጅ አለ፤
የሚከዳህ ሰው ቢኖር ግን ይገድልህ ዘንድ እርሱ ይቀድማል።
6በተመቸህ ጊዜ ወዳጅህን አትርሳ፤
ገንዘብም ብታገኝ አትተወው።
7መካር ሁሉ ምክርን ይመክራል፤
ነገር ግን ራሱን ይጠቅም ዘንድ የሚመክር ሰው አለ።
8ከሚመክርህ ሰው ልቡናህን ጠብቅ፤
ስለ ራሱ ይመክርሃልና፤ ይወድድህም ዘንድ አስቀድመህ ፍላጎቱን ዕወቅበት።
9ገንዘብህን የሚያጠፋብህን ነገር ያመጣብሃል#ግሪክ ሰባ. ሊ. ልዩነት ያሳያል።
በጎ ነገር አደረግህ ይልሃል፤
በተቸገርህም ጊዜ አይቶ ይስቅብሃል።
10ከሚጠባበቅህ ሰው ጋራ አትማከር፤
ከሚመቀኝህም ሰው ነገርህን ሰውር።
11ከሴት ጋር ስለሚያስቀናት ነገር አትናገር፤
ስለ ጦርነትም ከፈሪ ሰው ጋር አትማከር።
ስለ ትርፍም ከሻጭ ጋር አትማከር፤
ስለ ንግድ ነገርም ከነጋዴ ጋር አትማከር።
ስለ ምጽዋትም ከንፉግ ሰው ጋር አትማከር።
ዋጋን ስለ መመለስም ከከዳተኛ ጋር አትማከር፤
ስለ ሥራም ከሰነፍ ሰው ጋራ አትማከር፤
ሥራ ስለሚፈጸምበት ዓመትም ከምንደኛ ጋር አትማከር።
ስለ ጥበብም ከአላዋቂ ሰው ጋር አትማከር፤
ከዚህም ሁሉ ጋር ስለዚህ ነገር የምትማከረው አይኑር።
12ሃይማኖት እንዳለው#ግሪክ ሰባ. ሊ. “ሕግጋትን እንደሚጠብቅ” ይላል። ከምታውቀው፥ እግዚአብሔርንም ከሚፈራ፥
ልቡናውም እንደ ልብህ ከሆነ ጻድቅ ሰው ጋር ምክርህን ተናገር፤
ብታዝንም ከአንተ ጋር ያዝናል።
13እርስዋ ከሁሉ ይልቅ ታማኝህ ናትና፤
የልቡናህን ምክር አጽና።
14የሰው ልቡና ከሰባት ጠባቂዎች ይልቅ
የሚደርስበትን ነገር ፈጽማ ታስታውቀዋለችና።
15ከዚህ ሁሉ ጋር መንገድህን በእውነት ያቀናልህ ዘንድ፥
ወደ ልዑል እግዚአብሔር ለምን።
16የመፍቅድ ሁሉ መጀመሪያ ቃል ነው፤
የሥራም ሁሉ መጀመሪያ ምክር ነው።
17የሰው የልቡ ምልክት በአራቱ ወገን ይታያል።
18እነዚህም ኀዘንና ደስታ#ግሪክ ሰባ. ሊ. “ደግነትና ክፋት” ይላል። ሞትና ሕይወት ናቸው።
እነዚህንም ሁሉ አንደበት ያመጣቸዋል።
19ሁሉን የሚማር፥ ብዙም የሚያውቅ ሰው አለ፤
ነገር ግን ሰውነቱን መጥቀም አይችልም።
20በነገር የሚራቀቅ፥ ነገር ግን ራሱን የሚያስጠላ ሰው አለ።
እንደዚህ ያለውን ሰው ጥቅሙ ሁሉ ያልፈዋል።
21እግዚአብሔር ሞገስን አይሰጠውምና
ከጥበቡም ሁሉ ወጥትዋልና።
22በራሱ የሚራቀቅ፥
በቃሉም የዋህ የሚሆን ሰው አለ።
23ብልህ ሰው ወገኖቹን ይመክራቸዋል፤
ለዘመዶቹም ጥበብን ያስተምራቸዋል።#ግሪክ ሰባ. ሊ. “የማስተዋልም ፍሬ በአንደበቱ አለ” ይላል።
24ብልህ ሰው በበረከት ይጠግባል፤
ያዩትም ሰዎች ሁሉ ብፁዕ ይሉታል።
25የሰው ዘመኑ በቍጥር ነው፤
የእስራኤል ዘመን ግን የማይቈጠር ነው።
26ለወገኖቹ ጥበበኛ የሆነ ሰው ዋጋውን ያገኛል፤
ስሙም ለዘለዓለም ይኖራል።
27ልጄ ሆይ፥ በሕይወት ሳለህ ሰውነትህን ፈትናት፥
የሚጎዳትንም ዐውቀህ አትስጣት፤
28ሁሉ ለሰውነት የሚገባት አይደለምና፥
ሁሉም ደስ የሚያሰኛት አይደለምና፤
29ለመብል ሁሉ አትሰስት፤
ላየኸውም እህል ሁሉ አትሳሳ።
30ብዙ መብላት ደዌ ይሆናልና፤
ስስትም ጓታን ያበዛዋልና።
31ስስት የገደላቸው ሰዎች ብዙ ናቸው፥
መጥኖ የሚበላ ሰው ግን ሰውነቱ ጤነኛ ነው።
Currently Selected:
መጽሐፈ ሲራክ 37: አማ2000
ማድመቅ
ያጋሩ
ኮፒ

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ
መጽሐፈ ሲራክ 37
37
1ወዳጅ ያበጀ ሰው ሁሉ እኔም ወዳጁ ነኝ ይላል፤
ነገር ግን በከንቱ ለስም ወዳጅ የሚሆን ሰው አለ።
2በልቡናው ግን እስከሚሞትበት ቀን ድረስ ኀዘን ይኖራል፤
ጠላት የሚሆን ወዳጅም አለ።
3ክፉ ምኞት ሆይ! ከወዴት ተገኘሽ፤
በምድሩ ሁሉ ኀጢአትን መላሽ።
4በደስታህ ጊዜ የሚቀርብህ ወዳጅ አለ፤
ብትቸገር ግን እርሱ ጠላት ይሆንሃል።
5በበሽታህ ጊዜ ስለ ሆዱ የሚያዝንልህ ወዳጅ አለ፤
የሚከዳህ ሰው ቢኖር ግን ይገድልህ ዘንድ እርሱ ይቀድማል።
6በተመቸህ ጊዜ ወዳጅህን አትርሳ፤
ገንዘብም ብታገኝ አትተወው።
7መካር ሁሉ ምክርን ይመክራል፤
ነገር ግን ራሱን ይጠቅም ዘንድ የሚመክር ሰው አለ።
8ከሚመክርህ ሰው ልቡናህን ጠብቅ፤
ስለ ራሱ ይመክርሃልና፤ ይወድድህም ዘንድ አስቀድመህ ፍላጎቱን ዕወቅበት።
9ገንዘብህን የሚያጠፋብህን ነገር ያመጣብሃል#ግሪክ ሰባ. ሊ. ልዩነት ያሳያል።
በጎ ነገር አደረግህ ይልሃል፤
በተቸገርህም ጊዜ አይቶ ይስቅብሃል።
10ከሚጠባበቅህ ሰው ጋራ አትማከር፤
ከሚመቀኝህም ሰው ነገርህን ሰውር።
11ከሴት ጋር ስለሚያስቀናት ነገር አትናገር፤
ስለ ጦርነትም ከፈሪ ሰው ጋር አትማከር።
ስለ ትርፍም ከሻጭ ጋር አትማከር፤
ስለ ንግድ ነገርም ከነጋዴ ጋር አትማከር።
ስለ ምጽዋትም ከንፉግ ሰው ጋር አትማከር።
ዋጋን ስለ መመለስም ከከዳተኛ ጋር አትማከር፤
ስለ ሥራም ከሰነፍ ሰው ጋራ አትማከር፤
ሥራ ስለሚፈጸምበት ዓመትም ከምንደኛ ጋር አትማከር።
ስለ ጥበብም ከአላዋቂ ሰው ጋር አትማከር፤
ከዚህም ሁሉ ጋር ስለዚህ ነገር የምትማከረው አይኑር።
12ሃይማኖት እንዳለው#ግሪክ ሰባ. ሊ. “ሕግጋትን እንደሚጠብቅ” ይላል። ከምታውቀው፥ እግዚአብሔርንም ከሚፈራ፥
ልቡናውም እንደ ልብህ ከሆነ ጻድቅ ሰው ጋር ምክርህን ተናገር፤
ብታዝንም ከአንተ ጋር ያዝናል።
13እርስዋ ከሁሉ ይልቅ ታማኝህ ናትና፤
የልቡናህን ምክር አጽና።
14የሰው ልቡና ከሰባት ጠባቂዎች ይልቅ
የሚደርስበትን ነገር ፈጽማ ታስታውቀዋለችና።
15ከዚህ ሁሉ ጋር መንገድህን በእውነት ያቀናልህ ዘንድ፥
ወደ ልዑል እግዚአብሔር ለምን።
16የመፍቅድ ሁሉ መጀመሪያ ቃል ነው፤
የሥራም ሁሉ መጀመሪያ ምክር ነው።
17የሰው የልቡ ምልክት በአራቱ ወገን ይታያል።
18እነዚህም ኀዘንና ደስታ#ግሪክ ሰባ. ሊ. “ደግነትና ክፋት” ይላል። ሞትና ሕይወት ናቸው።
እነዚህንም ሁሉ አንደበት ያመጣቸዋል።
19ሁሉን የሚማር፥ ብዙም የሚያውቅ ሰው አለ፤
ነገር ግን ሰውነቱን መጥቀም አይችልም።
20በነገር የሚራቀቅ፥ ነገር ግን ራሱን የሚያስጠላ ሰው አለ።
እንደዚህ ያለውን ሰው ጥቅሙ ሁሉ ያልፈዋል።
21እግዚአብሔር ሞገስን አይሰጠውምና
ከጥበቡም ሁሉ ወጥትዋልና።
22በራሱ የሚራቀቅ፥
በቃሉም የዋህ የሚሆን ሰው አለ።
23ብልህ ሰው ወገኖቹን ይመክራቸዋል፤
ለዘመዶቹም ጥበብን ያስተምራቸዋል።#ግሪክ ሰባ. ሊ. “የማስተዋልም ፍሬ በአንደበቱ አለ” ይላል።
24ብልህ ሰው በበረከት ይጠግባል፤
ያዩትም ሰዎች ሁሉ ብፁዕ ይሉታል።
25የሰው ዘመኑ በቍጥር ነው፤
የእስራኤል ዘመን ግን የማይቈጠር ነው።
26ለወገኖቹ ጥበበኛ የሆነ ሰው ዋጋውን ያገኛል፤
ስሙም ለዘለዓለም ይኖራል።
27ልጄ ሆይ፥ በሕይወት ሳለህ ሰውነትህን ፈትናት፥
የሚጎዳትንም ዐውቀህ አትስጣት፤
28ሁሉ ለሰውነት የሚገባት አይደለምና፥
ሁሉም ደስ የሚያሰኛት አይደለምና፤
29ለመብል ሁሉ አትሰስት፤
ላየኸውም እህል ሁሉ አትሳሳ።
30ብዙ መብላት ደዌ ይሆናልና፤
ስስትም ጓታን ያበዛዋልና።
31ስስት የገደላቸው ሰዎች ብዙ ናቸው፥
መጥኖ የሚበላ ሰው ግን ሰውነቱ ጤነኛ ነው።