መጽሐፈ ሲራክ 36
36
1ይፈትኑት ዘንድ ነው እንጂ፥
እግዚአብሔርን የሚፈራ ሰውን መከራ አያገኘውም፤
ከመከራዪቱም ይድናል።
2ብልህ ሰው መጽሐፍ መስማትን ይወድዳል፤
የሚጠራጠርና በመጽሐፉ የማያምን ሰው ግን በጥቅል ነፋስ መካከል እንደምትንጓለል መርከብ ይሆናል።
3ብልህ ሰው አምኖ በእግዚአብሔር ሕግ ይገዛል፤
እግዚአብሔርም የታመነ ወዳጁ ይሆናል፤ ደስም ያሰኘዋል።
4የምትናገረውን ነገርህን አዘጋጅተህ አድምጥ፤
የምታደርገውንም ምክር አጽንተህ ተናገር።
5የሰነፍ ሰው ልቡና እንደ ሰረገላ መንኰራኵር ነው፤
የፈሪ ሰው ምክርም እንደምትሽከረከር እንዝርት ነው።
6ጮሌ ፈረስ እንደ በጎ#ግሪክ ሰባ. ሊ. “አሽሟጣጭ” ይላል። ወዳጅ ነው።
በሚጋልበውም ሁሉ በታች ያሽካካል።
7የዓመቱ ቀን ሁሉ በፀሐይ ብርሃን ጸንቶ ሲኖር፥
አንዲቱ ቀን ካንዲቱ ቀን በምን ትበልጣለች?
8ቀኑ ሁሉ በእግዚአብሔር ትእዛዝ ይለያል፤
የበዓላቱም ጊዜ በቍጥሩ ይታወቃል።
9ከቀኑም የቀደሰውና ያከበረው አለ።
ከእነርሱም በየጊዜያቸውና በየቍጥራቸው ክረምትንና መጸውን፥ በጋንም#“ክረምትንና መጸውን፥ በጋንም” የሚለው በግሪኩ የለም። ለየ።
10እኛ ሁላችን የአዳም ልጆች ከመሬት ተገኘን፤
አዳምም ከመሬት ተፈጠረ።
11እግዚአብሔርም በጥበቡ ብዛት ለያቸው፤
በየመንገዳቸውም አዘጋጃቸው።
12ከእነርሱም የባረካቸውና ከፍ ከፍ ያደረጋቸው አሉ፤
ከእነርሱም የቀደሳቸውና የተገለጠላቸው አሉ።
ከእነርሱም የረገማቸውና ያጐሳቈላቸው አሉ፤
እንደ ሥራቸውም የወነጀላቸው አሉ።
13እኛ ሁላችን በእርሱ ዘንድ በሸክላ ሠሪ እጅ እንዳለ ጭቃ፥ ነን፤#ግሪክ ሰባ. ሊ. “ደስ እንደሚያሰኘው አድርጎ ይሠራው ዘንድ በሸክላ ሠሪ እጅ እንደ ጭቃ ነን” ይላል።
ፍጥረቱ ሁሉ በመንገዶቹ ይሄዳል፤ ሰውም እንዲሁ በፈጣሪው እጅ ነው፤
ለሁሉም እንደ ሥራው ይከፍለዋል።
14የክፋት ተቃራኒዋ በጎነት ናት፤
የሞትም ተቃራኒዋ ሕይወት ናት፤
እንደዚሁ የጻድቅ ተቃራኒው ኃጥእ ነው።
15ከዚህ ሁሉ ጋር የልዑልን ፍጥረቶች ተመልከት፤
አንዱ የሌላው ተቃራኒ ሆኖ ሁለት ሁለት ናቸው።
16እኔ ግን ከሁሉ በኋላ ተነሥቼ ይኽን ነገር አሰብሁት፥
ከጥንቱም ጀምሬ መረመርሁት።
17አቤቱ በስምህ የተጠሩ ወገኖችህን ይቅር በል፤
የበኵር ልጄ ያልሃቸው እስራኤልንም ይቅር በል።
18ቅድስት ከተማህን፥
ማረፊያ ቦታህን ኢየሩሳሌምንም ይቅር በል።
19ጽዮንንም የቃልህን በረከት ሙላት፤
ክብርህንም በወገኖችህ ላይ ሙላ።
20አስቀድሞ ለፈጠርሃቸው ሕግህን ስጣቸው፤
ለስምህም ነቢያትን አስነሣ።
21ነቢያትህን ያምኗቸው ዘንድ ተስፋ ላደረጉህ ዋጋቸውን ስጣቸው።
አቤቱ የባሮችህ የነቢያትን ጸሎታቸውን ስማ፤
22የአሮንንም በረከት በሕዝብህ ላይ አሳድር፤
በምድር የሚኖሩ ሰዎች ሁሉ ዘለዓለማዊ አምላክ እግዚአብሔር አንተ ብቻ እንደ ሆንህ ይወቁ።
23እህል ሁሉ ይበላል፤ ወደ ሆድም ይወርዳል፤
ነገር ግን ከእህል የሚጣፍጥ እህል አለ።
24የእህልን ጣዕም ሁሉ ጕሮሮ ይለየዋል፥
እንደዚሁም ሁሉ የጠቢብ ሰው ልብ የሐሰት ነገርን ይለያል።
25ክፉ ልቡና ኀዘንን ያመጣል፤
ብዙ መከራ የተቀበለ ሰውም ትዕግሥትን ይለምደዋል።
26ወንድ ሁሉ ሚስት ያገባል፤
ነገር ግን ከሴት የምትሻል ሴት አለች።
27የሴት ውበቷ ፊትን ያበራዋል፤
ከሰው ፈቃድ ሁሉ እርሷ ትበልጣለች።
28የዋህ ብትሆን፥ ቃሏም ያማረ ቢሆን፤
ባሏ እንደ ሌሎች ሰዎች አይደለም።
29ረዳቱ፥ መደገፊያ ምሰሶውም ናትና፥
ልባም ሴትን ያገባ ሰው ደስታውን አገኘ።
30ቅጥር የሌለው ቤት ገንዘቡ እንዲሠረቅ፥
እንደዚሁም ሚስት የሌለችው ሰው ተቸግሮ ይኖራል።
31ከከተማ ወደ ከተማ የሚዞር ሌባን የሚዋሰው ማን ነው?
ልጆች የሌሉት፥ ንብረትም የሌለውና በመሸበት የሚያድር ሰውም እንዲሁ ነው።
Currently Selected:
መጽሐፈ ሲራክ 36: አማ2000
ማድመቅ
ያጋሩ
ኮፒ

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ
መጽሐፈ ሲራክ 36
36
1ይፈትኑት ዘንድ ነው እንጂ፥
እግዚአብሔርን የሚፈራ ሰውን መከራ አያገኘውም፤
ከመከራዪቱም ይድናል።
2ብልህ ሰው መጽሐፍ መስማትን ይወድዳል፤
የሚጠራጠርና በመጽሐፉ የማያምን ሰው ግን በጥቅል ነፋስ መካከል እንደምትንጓለል መርከብ ይሆናል።
3ብልህ ሰው አምኖ በእግዚአብሔር ሕግ ይገዛል፤
እግዚአብሔርም የታመነ ወዳጁ ይሆናል፤ ደስም ያሰኘዋል።
4የምትናገረውን ነገርህን አዘጋጅተህ አድምጥ፤
የምታደርገውንም ምክር አጽንተህ ተናገር።
5የሰነፍ ሰው ልቡና እንደ ሰረገላ መንኰራኵር ነው፤
የፈሪ ሰው ምክርም እንደምትሽከረከር እንዝርት ነው።
6ጮሌ ፈረስ እንደ በጎ#ግሪክ ሰባ. ሊ. “አሽሟጣጭ” ይላል። ወዳጅ ነው።
በሚጋልበውም ሁሉ በታች ያሽካካል።
7የዓመቱ ቀን ሁሉ በፀሐይ ብርሃን ጸንቶ ሲኖር፥
አንዲቱ ቀን ካንዲቱ ቀን በምን ትበልጣለች?
8ቀኑ ሁሉ በእግዚአብሔር ትእዛዝ ይለያል፤
የበዓላቱም ጊዜ በቍጥሩ ይታወቃል።
9ከቀኑም የቀደሰውና ያከበረው አለ።
ከእነርሱም በየጊዜያቸውና በየቍጥራቸው ክረምትንና መጸውን፥ በጋንም#“ክረምትንና መጸውን፥ በጋንም” የሚለው በግሪኩ የለም። ለየ።
10እኛ ሁላችን የአዳም ልጆች ከመሬት ተገኘን፤
አዳምም ከመሬት ተፈጠረ።
11እግዚአብሔርም በጥበቡ ብዛት ለያቸው፤
በየመንገዳቸውም አዘጋጃቸው።
12ከእነርሱም የባረካቸውና ከፍ ከፍ ያደረጋቸው አሉ፤
ከእነርሱም የቀደሳቸውና የተገለጠላቸው አሉ።
ከእነርሱም የረገማቸውና ያጐሳቈላቸው አሉ፤
እንደ ሥራቸውም የወነጀላቸው አሉ።
13እኛ ሁላችን በእርሱ ዘንድ በሸክላ ሠሪ እጅ እንዳለ ጭቃ፥ ነን፤#ግሪክ ሰባ. ሊ. “ደስ እንደሚያሰኘው አድርጎ ይሠራው ዘንድ በሸክላ ሠሪ እጅ እንደ ጭቃ ነን” ይላል።
ፍጥረቱ ሁሉ በመንገዶቹ ይሄዳል፤ ሰውም እንዲሁ በፈጣሪው እጅ ነው፤
ለሁሉም እንደ ሥራው ይከፍለዋል።
14የክፋት ተቃራኒዋ በጎነት ናት፤
የሞትም ተቃራኒዋ ሕይወት ናት፤
እንደዚሁ የጻድቅ ተቃራኒው ኃጥእ ነው።
15ከዚህ ሁሉ ጋር የልዑልን ፍጥረቶች ተመልከት፤
አንዱ የሌላው ተቃራኒ ሆኖ ሁለት ሁለት ናቸው።
16እኔ ግን ከሁሉ በኋላ ተነሥቼ ይኽን ነገር አሰብሁት፥
ከጥንቱም ጀምሬ መረመርሁት።
17አቤቱ በስምህ የተጠሩ ወገኖችህን ይቅር በል፤
የበኵር ልጄ ያልሃቸው እስራኤልንም ይቅር በል።
18ቅድስት ከተማህን፥
ማረፊያ ቦታህን ኢየሩሳሌምንም ይቅር በል።
19ጽዮንንም የቃልህን በረከት ሙላት፤
ክብርህንም በወገኖችህ ላይ ሙላ።
20አስቀድሞ ለፈጠርሃቸው ሕግህን ስጣቸው፤
ለስምህም ነቢያትን አስነሣ።
21ነቢያትህን ያምኗቸው ዘንድ ተስፋ ላደረጉህ ዋጋቸውን ስጣቸው።
አቤቱ የባሮችህ የነቢያትን ጸሎታቸውን ስማ፤
22የአሮንንም በረከት በሕዝብህ ላይ አሳድር፤
በምድር የሚኖሩ ሰዎች ሁሉ ዘለዓለማዊ አምላክ እግዚአብሔር አንተ ብቻ እንደ ሆንህ ይወቁ።
23እህል ሁሉ ይበላል፤ ወደ ሆድም ይወርዳል፤
ነገር ግን ከእህል የሚጣፍጥ እህል አለ።
24የእህልን ጣዕም ሁሉ ጕሮሮ ይለየዋል፥
እንደዚሁም ሁሉ የጠቢብ ሰው ልብ የሐሰት ነገርን ይለያል።
25ክፉ ልቡና ኀዘንን ያመጣል፤
ብዙ መከራ የተቀበለ ሰውም ትዕግሥትን ይለምደዋል።
26ወንድ ሁሉ ሚስት ያገባል፤
ነገር ግን ከሴት የምትሻል ሴት አለች።
27የሴት ውበቷ ፊትን ያበራዋል፤
ከሰው ፈቃድ ሁሉ እርሷ ትበልጣለች።
28የዋህ ብትሆን፥ ቃሏም ያማረ ቢሆን፤
ባሏ እንደ ሌሎች ሰዎች አይደለም።
29ረዳቱ፥ መደገፊያ ምሰሶውም ናትና፥
ልባም ሴትን ያገባ ሰው ደስታውን አገኘ።
30ቅጥር የሌለው ቤት ገንዘቡ እንዲሠረቅ፥
እንደዚሁም ሚስት የሌለችው ሰው ተቸግሮ ይኖራል።
31ከከተማ ወደ ከተማ የሚዞር ሌባን የሚዋሰው ማን ነው?
ልጆች የሌሉት፥ ንብረትም የሌለውና በመሸበት የሚያድር ሰውም እንዲሁ ነው።