መጽ​ሐፈ ሲራክ 23

23
ከኀ​ጢ​አት ስለ መራቅ ጸሎት
1አቤቱ፥ አባቴ፥ የሕ​ይ​ወ​ቴም ፈጣሪ፥
በእ​ነ​ርሱ ምክር አት​ጣ​ለኝ፥
በእ​ነ​ር​ሱም እን​ዳ​ል​ጠፋ አት​ለ​የኝ፤
2ልቡ​ና​ዬን ማን በመ​ከ​ረ​ልኝ?
ድን​ቍ​ር​ና​ዬም ይተ​ወኝ ዘንድ፥ በተ​ና​ገ​ሩ​ብ​ኝም ነገር ድል እን​ዳ​ይ​ነ​ሱኝ፥ ለል​ቡ​ናዬ ጥበ​ብን ማን ባስ​ተ​ማ​ራት?
3በደሌ እን​ዳ​ይ​በ​ዛ​ብኝ፥ ኀጢ​አ​ቴም እን​ዳ​ይ​በ​ረ​ክ​ት​ብኝ፥
በጠ​ላ​ቶ​ችም ፊት እን​ዳ​ል​ወ​ድቅ፥
ጠላ​ቶ​ችም በእኔ ጥፋት ደስ እን​ዳ​ይ​ላ​ቸው፥
4ጌታዬ፥ አባቴ፥ የሕ​ይ​ወቴ ፈጣሪ ሆይ፥
ዐይ​ኔን የሚ​ያ​ስ​ታ​ትን ነገር አታ​ም​ጣ​ብኝ።
5መጐ​ም​ጀ​ት​ንም ከእኔ አር​ቅ​ልኝ።
6ጥጋብ አይ​ም​ጣ​ብኝ፤ ቍን​ጣ​ንም#ግሪክ ሰባ. ሊ. “ፍት​ወተ ሥጋ” ይላል። አያ​ቀ​ና​ጣኝ፤
ለክፉ ሰውም አሳ​ል​ፈህ አት​ስ​ጠኝ።
አን​ደ​በ​ትን ስለ መግ​ራት
7ልጆች ሆይ፥ የአ​ን​ደ​በ​ቴን ምክር ስሙኝ፤
ቃሌን የጠ​በቀ አይ​ሰ​ነ​ካ​ከ​ልም፤ አን​ደ​በ​ቱ​ንም የጠ​በቀ አይ​ወ​ድ​ቅም።
8ኀጢ​አ​ተኛ በስ​ን​ፍ​ናው ይያ​ዛል፤
ተሳ​ዳ​ቢና ትዕ​ቢ​ተ​ኛም በዚሁ ይሰ​ነ​ካ​ከ​ላሉ።
9ልጄ ሆይ፥ ለአ​ፍህ መሐ​ላን አታ​ስ​ለ​ም​ደው፤
በማ​ል​ህም ጊዜ የቅ​ዱ​ሱን ስም በሐ​ሰት አት​ጥራ።
10ሁል​ጊዜ እየ​ተ​መ​ረ​መረ የሚ​ገ​ረፍ ባሪያ ቍስሉ እን​ደ​ማ​ይ​ደ​ርቅ፥
እን​ደ​ዚሁ ሲምል ሁል​ጊዜ የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ስም በሐ​ሰት የሚ​ጠራ ሰው ከኀ​ጢ​አት አይ​ነ​ጻም።
11መሐ​ላን የሚ​ያ​በዛ ሰው ኀጢ​አቱ ብዙ ነው፥
ከቤ​ቱም መቅ​ሠ​ፍት አይ​ር​ቅም፤
ቢያ​ረ​ጅም#ግሪኩ “በስ​ሕ​ተት ኀጢ​አት ቢሠራ” ይላል። ኀጢ​አቱ አይ​ተ​ወ​ውም፤
ቸል ቢልም ኀጢ​አቱ እጥፍ ይሆ​ን​በ​ታል፤
ፍዳው በቤቱ ሞል​ት​ዋ​ልና ስለ ማለ እው​ነ​ተኛ አይ​ባ​ልም።
12ሞትን የም​ታ​መ​ጣው ቃል አለች፤
በያ​ዕ​ቆ​ብም ርስት አት​ኖ​ርም፤
ይህ ሁሉ በጻ​ድ​ቃን ዘንድ የለም፤ በኀ​ጢ​አ​ትም አይ​ሰ​ነ​ካ​ከ​ሉም።
13በው​ስጡ ብዙ ኀጢ​አት አለና፥
ከአ​ን​ደ​በ​ትህ የመ​ዘ​ባ​በት ነገር አይ​ውጣ።
14አባ​ት​ህ​ንና እና​ት​ህን ዐስ​ባ​ቸው፥
መኳ​ን​ን​ቶ​ች​ህ​ንም አገ​ል​ግል፤#ግሪኩ “በታ​ላ​ላ​ቆች መካ​ከል በተ​ቀ​መ​ጥህ ጊዜ አባ​ት​ህ​ንና እና​ት​ህን ዐስ​ባ​ቸው” ይላል።
በፊ​ታ​ቸ​ውም አት​ሳት፤
ባል​ተ​ወ​ለ​ድሁ እን​ዳ​ትል፥
የተ​ወ​ለ​ድ​ህ​በ​ት​ንም ቀን እን​ዳ​ት​ረ​ግም በስ​ን​ፍ​ናህ እን​ዳ​ት​ጠላ ሁን።
15በሰው ላይ መሳ​ለ​ቅን የለ​መደ ሰው፥
መላ ሕይ​ወ​ቱን ብልህ አይ​ሆ​ንም።
ስለ ዝሙት ኀጢ​አት
16ኀጢ​አ​ትን የሚ​ያ​መ​ጧት ሁለት ናቸው፤
ሦስ​ተ​ኛው ግን ሞትን ያመ​ጣል፤
ቍጡ ሰው​ነት እን​ደ​ሚ​ቃ​ጠል እሳት ናት፤
እስ​ክ​ታ​ሰ​ጥ​መ​ውም ድረስ አት​በ​ር​ድም፤
በሰ​ው​ነ​ቱም የሚ​ሰ​ስን ሰው እሳ​ትን እስ​ኪ​ያ​ቀ​ጣ​ጥ​ላት ድረስ አይ​ተ​ውም።
17ለሴ​ሰኛ ሰው እህሉ ሁሉ ይጣ​ፍ​ጠ​ዋል፤
እስ​ኪ​ሞ​ትም ድረስ አያ​ር​ፍም።
18ሚስ​ቱን ትቶ የሚ​ሄድ ሰው፥
በልቡ “ጊዜው ጨለማ ነው፤ የሚ​ያ​የኝ የለም፤ አጥር ይጋ​ር​ደ​ኛል፤
ከዚህ በኋላ ምን እፈ​ራ​ለሁ? የሚ​ያ​ው​ቀ​ኝም የለም፤
ልዑ​ልም ኀጢ​አ​ቴን ይዘ​ነ​ጋ​ል​ኛል፤ አያ​ስ​ብ​ብ​ኝ​ምም” ይላል።
19ነገር ግን እን​ዳ​ያ​የው የሰው ዐይ​ንን ይፈ​ራል፤
የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርም ዐይን ከፀ​ሐይ መቶ ሺህ ጊዜ እን​ዲ​በራ፥
የሰ​ው​ንም ሥራ ሁሉ እን​ደ​ሚ​ያይ፥
ተሰ​ውሮ የሚ​ሠ​ራ​ንም ሥራ ሁሉ እን​ደ​ሚ​ያ​ውቅ አያ​ው​ቅም።
20ሁሉም ከመ​ፈ​ጠሩ በፊት በእ​ርሱ ዘንድ የታ​ወቀ ነው፤
ከጨ​ረ​ሰም በኋላ እን​ዲህ ያደ​ር​ገ​ዋል።
21በከ​ተ​ማም መካ​ከል ይበ​ቀ​ለ​ዋል፤
ባል​ጠ​ረ​ጠ​ረ​በ​ትም ቦታ ያጠ​ፋ​ዋል።
22ባሏን ትታ የም​ት​ሄድ ሴት እን​ዲሁ ናት፤
ከሌላ ወንድ ልጅን ትወ​ል​ዳ​ለች።
23በእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔር አን​ዲት ክህ​ደት አደ​ረ​ገች፤
ሁለ​ተ​ኛም ባሏን ከዳ​ችው፥
ሦስ​ተ​ኛም በሴ​ሰ​ኝ​ነ​ትዋ ሰረ​ቀች፤
ከሌላ ወን​ድም ልጅን ወለ​ደች።
24እን​ዲህ ያለ​ችው ሴት ቷረ​ዳ​ለች፤
በል​ጆ​ች​ዋም ትገ​ረ​ፋ​ለች።
25ዘሮ​ችዋ ይጠ​ፋሉ፤
ቅር​ን​ጫ​ፎ​ች​ዋም አያ​ፈ​ሩም።
26ስም አጠ​ራ​ሯም የተ​ረ​ገመ ይሆ​ናል፤
ለቤ​ቷም መር​ገ​ምን ታወ​ር​ሳ​ለች፤
መር​ገ​ም​ዋና ውር​ደቷ ለዘ​ለ​ዓ​ለሙ አይ​ጠ​ፋም።
27ያያት ሁሉ እግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ርን ከመ​ፍ​ራት የሚ​በ​ልጥ፥
የእ​ግ​ዚ​አ​ብ​ሔ​ር​ንም ሕግ ከመ​ጠ​በቅ የሚ​ጣ​ፍጥ እን​ደ​ሌለ ያው​ቃል።

ማድመቅ

ያጋሩ

ኮፒ

None

ያደመቋቸው ምንባቦች በሁሉም መሣሪያዎችዎ ላይ እንዲቀመጡ ይፈልጋሉ? ይመዝገቡ ወይም ይግቡ