የሹሐ አገር ሰው የሆነው ቢልዳድ እንዲህ ሲል መልስ ሰጠ፦ ከአንደበትህ የሚወጡት ቃላት እንደ ዐውሎ ነፋስ ናቸው፤ እስከ መቼ ድረስ እንደዚህ አድርገህ ትናገራለህ? እግዚአብሔር ፍርድን ከቶ አያጣምምም፤ ሁሉን ቻይ አምላክ ሁልጊዜ ትክክለኛውን ነገር ያደርጋል። ልጆችህ እግዚአብሔርን በድለውት ከሆነ፥ እነርሱ ቅጣታቸውን አግኝተዋል ማለት ነው። ነገር ግን ወደ እግዚአብሔር ብትመለስ፥ ሁሉን ቻዩን አምላክ ብትለምነው፥ ቀጥተኛና ንጹሕ ከሆንክ፥ እርሱ ፈጥኖ ወደ ተገቢ ቦታህ ይመልስሃል። አጀማመርህ አነስተኛ መስሎ ቢታይም፥ የወደፊት ኑሮህ የተትረፈረፈ ይሆናል። “እስቲ የጥንቱን ትውልድ ጠይቅ የቀድሞ አባቶቻቸውን ልምድ ተመራመር። የእኛ ዕድሜ ገና ትንሽ በመሆኑ ምንም አናውቅም፤ ዕድሜአችንም እንደ ጥላ የሚያልፍ ነው። እነርሱ የሚያስተምሩህና የሚነግሩህ ካስተዋሉት አፍልቀው አይደለምን? በውኑ ረግረግ ባልሆነ ቦታ ደንገል ይበቅላልን? ውሃስ በሌለበት ቦታ ሸምበቆ ይለመልማልን? ይህ ካልሆነ አድገው ለመቈረጥ ከመብቃታቸው በፊት ከማንኛውም አረንጓዴ ተክል ቀድመው ይደርቃሉ። እግዚአብሔርን የሚረሱ ሰዎች ሁሉ ፍጻሜአቸው ልክ እንደዚሁ ነው፤ እግዚአብሔር የለም የሚሉ ሰዎች ተስፋቸው ይቈረጣል። እንደ ሸረሪት ድር በሚበጠስ ነገር ይታመናሉ፤ ተስፋ የሚያደርጉበት ነገር እንኳ ቢኖር በቀላሉ ይጠፋል። በሸረሪቱ ድር ላይ ቢደገፍ ጸንቶ አይቆምም፤ የሸረሪት ድሩን ቢጨብጥ ይበጠስበታል። “አረም በፀሐይ አቈጥቊጦ በአትክልት ቦታው እንደሚበዛ ክፉ ሰዎችም እንደዚሁ ይበዛሉ። ሥሮቹም በድንጋይ ካብ ላይ ይጠመጠማሉ፤ በየቋጥኙም ላይ ይጣበቃሉ። አንድ ሰው ከቦታው ቢነቅለው የነበረበት ቦታ አይታወቅም። አረሙም በዚህ ዐይነት ይደርቃል፤ ሌሎች አትክልቶችም ከመሬት ያቈጠቊጣሉ። “እግዚአብሔር ደጋግ ሰዎችን አይጥላቸውም፤ ክፉዎችንም አይረዳቸውም።
መጽሐፈ ኢዮብ 8 ያንብቡ
ያጋሩ
ሁሉንም ሥሪቶች ያነጻጽሩ: መጽሐፈ ኢዮብ 8:1-20
ጥቅሶችን ያስቀምጡ፣ ያለበይነመረብ ያንብቡ፣ አጫጭር የትምህርት ቪዲዮዎችን ይመልከቱ እና ሌሎችም!
ቤት
መጽሐፍ ቅዱስ
እቅዶች
ቪዲዮዎች