ኦሪት ዘሌዋውያን መግቢያ
መግቢያ
ኦሪት ዘሌዋውያን የሚያትተው በጥንታዊት እስራኤል ስለ ነበሩት የአምልኮ ደንቦችና ስለ ሃይማኖታዊ ሥርዓቶች ነው፤ እንዲሁም እነዚህን ሥርዓቶች በተግባር የመተርጐም ኀላፊነት ስለ ነበራቸው ካህናት ይገልጣል።
የመጽሐፉ ማእከላዊ ሐሳብ ስለ እግዚአብሔር ቅድስና የሚናገር ነው፤ እንዲሁም የእግዚአብሔር ሕዝብ ከዚሁ ቅዱስ ከሆነው ከእስራኤል አምላክ ጋር የቅርብ ግንኙነት ይኖራቸው ዘንድ፥ በእንዴት ያለ ሁኔታ ማምለክ እንደሚገባቸው ይዘረዝራል።
ከመጽሐፉ ውስጥ በጣም የታወቀው ትእዛዝ ኢየሱስ ሁለተኛው ታላቅ ትእዛዝ ብሎ የሠየመውና በም. 19 ቊ. 18 ላይ የሚገኘው ነው፤ እርሱም “ሰውን ሁሉ እንደ ራስህ አድርገህ ውደድ” የሚለው ነው።
አጠቃላይ የመጽሐፉ ይዘት
ሀ. የመባና የመሥዋዕት ሕግ 1፥1—7፥38
ለ. የአሮንና የልጆቹ የክህነት ሹመት 8፥1—10፥20
ሐ. ንጹሕ የሆነና ያልሆነ ነገር፥ እንዲሁም የመንጻት ሥርዓት 11፥1—15፥33
መ. የኃጢአት ስርየት ቀን 16፥1-34
ሠ. የቅድስና ሕይወትና የአምልኮ ሕግ 17፥1—27፥34
Nu markerat:
ኦሪት ዘሌዋውያን መግቢያ: አማ05
Märk
Dela
Kopiera
Vill du ha dina höjdpunkter sparade på alla dina enheter? Registrera dig eller logga in
© The Bible Society of Ethiopia, 2005
© የኢትዮጵያ መጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር፥ 1997
ኦሪት ዘሌዋውያን መግቢያ
መግቢያ
ኦሪት ዘሌዋውያን የሚያትተው በጥንታዊት እስራኤል ስለ ነበሩት የአምልኮ ደንቦችና ስለ ሃይማኖታዊ ሥርዓቶች ነው፤ እንዲሁም እነዚህን ሥርዓቶች በተግባር የመተርጐም ኀላፊነት ስለ ነበራቸው ካህናት ይገልጣል።
የመጽሐፉ ማእከላዊ ሐሳብ ስለ እግዚአብሔር ቅድስና የሚናገር ነው፤ እንዲሁም የእግዚአብሔር ሕዝብ ከዚሁ ቅዱስ ከሆነው ከእስራኤል አምላክ ጋር የቅርብ ግንኙነት ይኖራቸው ዘንድ፥ በእንዴት ያለ ሁኔታ ማምለክ እንደሚገባቸው ይዘረዝራል።
ከመጽሐፉ ውስጥ በጣም የታወቀው ትእዛዝ ኢየሱስ ሁለተኛው ታላቅ ትእዛዝ ብሎ የሠየመውና በም. 19 ቊ. 18 ላይ የሚገኘው ነው፤ እርሱም “ሰውን ሁሉ እንደ ራስህ አድርገህ ውደድ” የሚለው ነው።
አጠቃላይ የመጽሐፉ ይዘት
ሀ. የመባና የመሥዋዕት ሕግ 1፥1—7፥38
ለ. የአሮንና የልጆቹ የክህነት ሹመት 8፥1—10፥20
ሐ. ንጹሕ የሆነና ያልሆነ ነገር፥ እንዲሁም የመንጻት ሥርዓት 11፥1—15፥33
መ. የኃጢአት ስርየት ቀን 16፥1-34
ሠ. የቅድስና ሕይወትና የአምልኮ ሕግ 17፥1—27፥34
Nu markerat:
:
Märk
Dela
Kopiera
Vill du ha dina höjdpunkter sparade på alla dina enheter? Registrera dig eller logga in
© The Bible Society of Ethiopia, 2005
© የኢትዮጵያ መጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር፥ 1997