1
የሉቃስ ወንጌል 5:4
አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም
አማ05
ንግግሩንም ከጨረሰ በኋላ ስምዖንን፦ “ጀልባዋን ወደ ጥልቁ ባሕር ራቅ አድርገህ አንተና ጓደኞችህ ዓሣ ለማጥመድ መረባችሁን ጣሉ፤” አለው።
Konpare
Eksplore የሉቃስ ወንጌል 5:4
2
የሉቃስ ወንጌል 5:5-6
ስምዖንም “መምህር ሆይ! ሌሊቱን ሙሉ ስንደክም አድረን ምንም አልያዝንም፤ አንተ ካልክ ግን፥ እነሆ! መረቡን እንጥላለን፤” አለው። መረቡን በጣሉ ጊዜ መረቡ እስኪቀደድ ድረስ እጅግ ብዙ ዓሣ ያዙ።
Eksplore የሉቃስ ወንጌል 5:5-6
3
የሉቃስ ወንጌል 5:16
እርሱ ግን በየጊዜው ብቻውን ወደ በረሓ እየሄደ ይጸልይ ነበር።
Eksplore የሉቃስ ወንጌል 5:16
4
የሉቃስ ወንጌል 5:32
እኔ የመጣሁት ኃጢአተኞችን ወደ ንስሓ ለመጥራት ነው እንጂ ጻድቃንን ለመጥራት አይደለም።”
Eksplore የሉቃስ ወንጌል 5:32
5
የሉቃስ ወንጌል 5:8
ስምዖን ጴጥሮስ ይህን ባየ ጊዜ በኢየሱስ ፊት ተንበርክኮ፥ “ጌታ ሆይ፥ እኔ ኃጢአተኛ ስለ ሆንኩ ወደ እኔ አትቅረብ!” አለው።
Eksplore የሉቃስ ወንጌል 5:8
6
የሉቃስ ወንጌል 5:31
ኢየሱስም እንዲህ ሲል መለሰላቸው፦ “በሽተኞች እንጂ ጤነኞች ሐኪም አያስፈልጋቸውም፤
Eksplore የሉቃስ ወንጌል 5:31
7
የሉቃስ ወንጌል 5:11
እነርሱም ጀልባዎቹን ወደ ምድር ካስጠጉ በኋላ ሁሉን ነገር ትተው የኢየሱስ ተከታዮች ሆኑ።
Eksplore የሉቃስ ወንጌል 5:11
8
የሉቃስ ወንጌል 5:12-13
አንድ ቀን ኢየሱስ በአንዲት ከተማ ውስጥ ሳለ ገላውን ለምጽ የወረሰው አንድ ሰው ወደ እርሱ መጣ፤ ኢየሱስን ባየው ጊዜ በግንባሩ ተደፍቶ ጌታ ሆይ፥ “ብትፈቅድስ ልታነጻኝ ትችላለህ፤” ሲል ለመነው። ኢየሱስም እጁን ዘርግቶ ዳሰሰውና “ፈቅጃለሁ ንጻ!” አለው። ሰውዬውም ወዲያውኑ ከለምጹ ነጻ።
Eksplore የሉቃስ ወንጌል 5:12-13
9
የሉቃስ ወንጌል 5:15
የኢየሱስ ዝና ግን ከምንጊዜውም ይበልጥ ተሰማ፤ ብዙ ሰዎችም እርሱን ለመስማትና ከበሽታቸውም ለመዳን ፈልገው ይሰበሰቡ ነበር።
Eksplore የሉቃስ ወንጌል 5:15
Akèy
Bib
Plan yo
Videyo