የማርቆስ ወንጌል መግቢያ
መግቢያ
የማርቆስ ወንጌል “ይህ የእግዚአብሔር ልጅ የኢየሱስ ክርስቶስ የምሥራች ቃል መጀመሪያ ነው” በማለት ይነሣል፤ በዚህ ወንጌል ውስጥ ኢየሱስ የሥራና የሥልጣን ሰው በመሆን ቀርቦአል፤ ሥልጣኑም በትምህርቱ፥ በአጋንንት ላይ ባለው ኀይልና የሰውን ኃጢአት ይቅር በማለቱ ታይቶአል። ኢየሱስ “ሰዎችን ከኃጢአት ባርነት ነጻ በማውጣት ሕይወቴን ቤዛ አድርጌ ለመስጠት የመጣሁ የሰው ልጅ ነኝ” በማለት ራሱ ተናግሮአል።
ማርቆስ የኢየሱስን ታሪክ ያቀረበው፥ ቀጥተኛና ኀይልን በተሞላ መንገድ ሲሆን ያተኰረውም በኢየሱስ ቃልና ትምህርት ላይ ሳይሆን ባከናወናቸው ድንቅ ሥራዎች ላይ ነበር። ስለ መጥምቁ ዮሐንስ ታሪክ፥ ስለ ኢየሱስ ጥምቀትና ፈተና አጠር ያለ መግቢያ ከሰጠ በኋላ ጸሐፊው ስለ ኢየሱስ የማስተማርና የመፈወስ አገልግሎት ይተነትናል። ከጊዜ በኋላ የኢየሱስ ተከታዮች ኢየሱስን በበለጠ ሁኔታ እያወቁ በሄዱ መጠን የኢየሱስ ተቃዋሚዎችም ይበልጡን እየጠሉት ሄዱ። የመጨረሻዎቹ ምዕራፎች በኢየሱስ ሕይወት በመጨረሻው ሳምንት ውስጥ ስለ ተፈጸሙት ድርጊቶች፥ በተለይም ስለ ስቅለቱና ስለ ትንሣኤው የሚተርኩ ናቸው።
በወንጌሉ መጨረሻ ላይ በቅንፍ የተመለከቱት ሁለት ክፍሎች በአንዳንድ ቅጂዎች ብቻ የሚገኙ ናቸው።
አጠቃላይ የመጽሐፉ ይዘት
የወንጌሉ መጀመሪያ 1፥1-13
ኢየሱስ አገልግሎቱን በገሊላ መጀመሩ 1፥14—9፥50
በኢየሩሳሌም ማገልገሉ 10፥1-52
በኢየሩሳሌምና በአካባቢዋ የመጨረሻ ሳምንት 11፥1—15፥47
የጌታ ትንሣኤ 16፥1-8
ከሞት የተነሣው ጌታ መገለጥና ዕርገቱ 16፥9-20
Sélection en cours:
የማርቆስ ወንጌል መግቢያ: አማ05
Surbrillance
Partager
Copier

Tu souhaites voir tes moments forts enregistrés sur tous tes appareils? Inscris-toi ou connecte-toi
© The Bible Society of Ethiopia, 2005
© የኢትዮጵያ መጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር፥ 1997
የማርቆስ ወንጌል መግቢያ
መግቢያ
የማርቆስ ወንጌል “ይህ የእግዚአብሔር ልጅ የኢየሱስ ክርስቶስ የምሥራች ቃል መጀመሪያ ነው” በማለት ይነሣል፤ በዚህ ወንጌል ውስጥ ኢየሱስ የሥራና የሥልጣን ሰው በመሆን ቀርቦአል፤ ሥልጣኑም በትምህርቱ፥ በአጋንንት ላይ ባለው ኀይልና የሰውን ኃጢአት ይቅር በማለቱ ታይቶአል። ኢየሱስ “ሰዎችን ከኃጢአት ባርነት ነጻ በማውጣት ሕይወቴን ቤዛ አድርጌ ለመስጠት የመጣሁ የሰው ልጅ ነኝ” በማለት ራሱ ተናግሮአል።
ማርቆስ የኢየሱስን ታሪክ ያቀረበው፥ ቀጥተኛና ኀይልን በተሞላ መንገድ ሲሆን ያተኰረውም በኢየሱስ ቃልና ትምህርት ላይ ሳይሆን ባከናወናቸው ድንቅ ሥራዎች ላይ ነበር። ስለ መጥምቁ ዮሐንስ ታሪክ፥ ስለ ኢየሱስ ጥምቀትና ፈተና አጠር ያለ መግቢያ ከሰጠ በኋላ ጸሐፊው ስለ ኢየሱስ የማስተማርና የመፈወስ አገልግሎት ይተነትናል። ከጊዜ በኋላ የኢየሱስ ተከታዮች ኢየሱስን በበለጠ ሁኔታ እያወቁ በሄዱ መጠን የኢየሱስ ተቃዋሚዎችም ይበልጡን እየጠሉት ሄዱ። የመጨረሻዎቹ ምዕራፎች በኢየሱስ ሕይወት በመጨረሻው ሳምንት ውስጥ ስለ ተፈጸሙት ድርጊቶች፥ በተለይም ስለ ስቅለቱና ስለ ትንሣኤው የሚተርኩ ናቸው።
በወንጌሉ መጨረሻ ላይ በቅንፍ የተመለከቱት ሁለት ክፍሎች በአንዳንድ ቅጂዎች ብቻ የሚገኙ ናቸው።
አጠቃላይ የመጽሐፉ ይዘት
የወንጌሉ መጀመሪያ 1፥1-13
ኢየሱስ አገልግሎቱን በገሊላ መጀመሩ 1፥14—9፥50
በኢየሩሳሌም ማገልገሉ 10፥1-52
በኢየሩሳሌምና በአካባቢዋ የመጨረሻ ሳምንት 11፥1—15፥47
የጌታ ትንሣኤ 16፥1-8
ከሞት የተነሣው ጌታ መገለጥና ዕርገቱ 16፥9-20
Sélection en cours:
:
Surbrillance
Partager
Copier

Tu souhaites voir tes moments forts enregistrés sur tous tes appareils? Inscris-toi ou connecte-toi
© The Bible Society of Ethiopia, 2005
© የኢትዮጵያ መጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር፥ 1997