1
የሐዋርያት ሥራ 2:38
አማርኛ አዲሱ መደበኛ ትርጉም
አማ05
ጴጥሮስም እንዲህ አላቸው፤ “ንስሓ ግቡ፤ ኃጢአታችሁም ይቅር እንዲባልላችሁ እያንዳንዳችሁ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተጠመቁ፤ የእግዚአብሔር ስጦታ የሆነውን መንፈስ ቅዱስንም ትቀበላላችሁ፤
Porovnat
Zkoumat የሐዋርያት ሥራ 2:38
2
የሐዋርያት ሥራ 2:42
እነርሱም የሐዋርያትን ትምህርት በመስማት፥ በኅብረት በመኖር፥ ማዕድን አብሮ በመብላትና በጸሎት ይተጉ ነበር።
Zkoumat የሐዋርያት ሥራ 2:42
3
የሐዋርያት ሥራ 2:4
ሁሉም በመንፈስ ቅዱስ ተሞሉ፤ መንፈስ ቅዱስ እንዲናገሩ በሰጣቸው ችሎታ መጠን በሌሎች ቋንቋዎች መናገር ጀመሩ።
Zkoumat የሐዋርያት ሥራ 2:4
4
የሐዋርያት ሥራ 2:2-4
በድንገት ብርቱ ዐውሎ ነፋስ የመሰለ ድምፅ ከሰማይ መጣ፤ የነበሩበትንም ቤት ሞላው። የእሳት ነበልባሎች የሚመስሉ ልሳኖች ታዩአቸው፤ ተከፋፍለውም በእያንዳንዳቸው ላይ ዐረፉባቸው። ሁሉም በመንፈስ ቅዱስ ተሞሉ፤ መንፈስ ቅዱስ እንዲናገሩ በሰጣቸው ችሎታ መጠን በሌሎች ቋንቋዎች መናገር ጀመሩ።
Zkoumat የሐዋርያት ሥራ 2:2-4
5
የሐዋርያት ሥራ 2:46-47
በየቀኑ በቤተ መቅደስ በአንድነት ይሰበሰቡ ነበር፤ በቤታቸውም እንጀራ እየቈረሱ በደስታና በጥሩ ልብ ይመገቡ ነበር፤ ጌታንም ያመሰግኑ ነበር፤ ሰውም ሁሉ ያከብራቸው ነበር፤ እግዚአብሔርም የሚድኑትን ሰዎች በየቀኑ ወደ ማኅበራቸው ይጨምር ነበር።
Zkoumat የሐዋርያት ሥራ 2:46-47
6
የሐዋርያት ሥራ 2:17
‘እግዚአብሔር በመጨረሻው ቀን እንዲህ ይሆናል ይላል፤ መንፈሴን በሰው ሁሉ ላይ አፈሳለሁ፤ ወንዶችና ሴቶች ልጆቻችሁ ትንቢት ይናገራሉ፤ ጐልማሶቻችሁም ራእይ ያያሉ፤ ሽማግሌዎቻችሁም ሕልም ያልማሉ።
Zkoumat የሐዋርያት ሥራ 2:17
7
የሐዋርያት ሥራ 2:44-45
አማኞች ሁሉ በአንድነት አብረው ይኖሩ ነበር፤ ያላቸውም ነገር ሁሉ የጋራ ነበር። ዕርሻቸውንና ሀብታቸውን እየሸጡ ገንዘቡን ለእያንዳንዱ እንደሚያስፈልገው ያከፋፍሉ ነበር።
Zkoumat የሐዋርያት ሥራ 2:44-45
8
የሐዋርያት ሥራ 2:21
የጌታን ስም የሚጠራ ሁሉ ይድናል።’
Zkoumat የሐዋርያት ሥራ 2:21
9
የሐዋርያት ሥራ 2:20
ታላቁና አስገራሚው የጌታ ቀን ከመምጣቱ በፊት፥ ፀሐይ ይጨልማል፤ ጨረቃም ደም ትመስላለች።
Zkoumat የሐዋርያት ሥራ 2:20
Domů
Bible
Plány
Videa