ሐዲስ ኪዳን በ 90 ቀናትናሙና

የማቴዎስ ወንጌል መግቢያ
ማቴዎስ አንዳንድ ግዜ ደግሞ ሌዊ በመባልም የሚጠራው ወንጌላዊ በሥራው ቀረጥ ሰብሳቢ ሲሆን ያላቸውን ሃብት ንብረት በሙሉ ትተው ኢየሱስን ከተከተሉ 12 ቱ ደቀ መዛሙርት መካከል አንዱ ነበር። ይህንን መጽሐፍ የጻፈው ከ 60-65 ዓ.ም እንደሆነ ይታመናል። ማቴዎስ የኢየሱስን ተአምራት፣ ትንሣኤ እና ዕርገትን ተመልክቷል።
ማቴዎስ መጽሐፉን ለአይሁዳዊያን እንደጻፈው በበርካታ የነገረ መለኮት ምሁራን ዘንድ ይታመናል። ይህንን ልንገምት የምንችልባቸው ሦስት ምክንያቶች ውስጥ አንደኛው ማቴዎስ ከ 60 የሚበልጡ የብሉይ ኪዳን ትንቢቶችን የጠቀሰ ሲሆን ሁለተኛው ኢየሱስን የ“የዳዊት ልጅ” በማለት መጥራቱ ነው ሶስተኛው ደግሞ የአይሁድን ባህል በሚጽፍ ወቅት ምንም አይነት ማብራሪያ አለመስጠቱ እንደ ምክንያት ይጠቀሳሉ። የማቴዎስ ወንጌል በአዲስ ኪዳን ቅደም ተከተል የመጀመሪያው ወንጌል ሆኖ ሳለ የተጻፈው ግን ከማርቆስ ወንጌል በኋላ ነው። እንዲያውም 97% የሚሆነው የማርቆስ ወንጌል በማቴዎስ ወንጌል ውስጥ ተካትቷል።
ስለዚህ እቅድ

በቀጣዩ 90 ቀናት ውስጥ የሐዲስ ኪዳንን 260 ምዕራፎች ከ ማቴዎስ ወንጌል በመጀመር የማርቆስ ወንጌልን ፣ የሉቃስ ወንጌልን ፣ የዮሐንስ ወንጌልን በማንበብ እስከ መጨረሻው መጽሐፍ የዮሐንስ ራእይ ድረስ ይዘልቃል።Journey through the 260 chapters of the New Testament over the next 90 days. From the gospels of Matthew, Mark, Luke, and John, all the way to the final book of Revelation, God will speak to you throughout the teachings of those who were transformed by our Savior.
More