ኦሪት ዘፍጥረት 6:9-14

ኦሪት ዘፍጥረት 6:9-14 አማ54

የኖኅ ትውልድ እንዲህ ነው። ኖኅም በትውልዱ ጻድቅ ፍጹምም ስው ነበረ ኖኅ አካሄዱን ከእግዚአብሔር ጋር አደረግ። ኖኅም ሦስት ልጆችን ሴምን ካምን ያፌትንም ወለደ። ምድርም በእግዚአብሔር ፊት ተበላሸ ምድርም ግፍን ተሞላች። እግዚአብሔርም ምድርን አየ፤ እነሆም ተበላሸች ሥጋን የለበሰ ሁሉ በምድር ላይ መንገዱን አበላሽቶ ነበርና። እግዚእብሔርም ኖኅን አለው፤ የሥጋ ሁሉ ፍጻሜ በፊቴ ደርሶአል ከእነርሱ የተነሣ ምድር በግፍ ተሞልታለችን እኔም እነሆ ከምድር ጋር አጠፋቸዋለሁ። ከጎፈር እንጨት መርከብን ለአንተ ሥራ በመርከቢቱም ጉርጆችን አድርግ በውስጥን በውጭም በቅጥራን ለቅልቃት።

ቪዲዮ ለ {{ዋቢ_ሰዉ}}