የጠራች ጠፈርን በህዋው ላይ አጸናት፤ የሰማይም መታየት በክብሩ ነው። ብርሃኑን ያሳይ ዘንድ ፀሐይን ያወጣል፤ የሰማይም ብርሃን ሥርዐቱ ድንቅ ነው ። በዋዕዩም ሀገሩን ያቃጥላል፤ ዋዕዩንስ ማን ይቋቋመዋል? ዋዕዩንም እሳት እንደሚነድድባት ምድጃ ያደርጋል፤ ፀሐይ ግን ከሦስት ጊዜ በላይ የበለጠ ተራሮችን ያቃጥላቸዋል። ከእርሱ የሚወጣው እሳታዊ ዋዕይ፥ የሚልከውም ብርሃን ዐይን ያጨልማል፤ የፈጠረው እግዚአብሔርም ታላቅ ነው፤ በቃሉም ፈጥኖ ይሄዳል።
መጽሐፈ ሲራክ 43 ያንብቡ
ያጋሩ
ሁሉንም ሥሪቶች ያነጻጽሩ: መጽሐፈ ሲራክ 43:1-5
ጥቅሶችን ያስቀምጡ፣ ያለበይነመረብ ያንብቡ፣ አጫጭር የትምህርት ቪዲዮዎችን ይመልከቱ እና ሌሎችም!
ቤት
መጽሐፍ ቅዱስ
እቅዶች
ቪዲዮዎች